የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከሐረሪ ክልል መንግስት ጋር በመተባበር ለአቅመ ደካሞች ያስገነባቸውን ቤቶች አስረከበ

Oct 27, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር፤ጥቅምት 16/2018 (ኢዜአ) ፡-የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከሐረሪ ክልል መንግስት ጋር በመተባበር በክልሉ ለአቅመ ደካሞች ያስገነባውን የመኖሪያ ቤት አጠናቆ አስረከበ።

በክልሉ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ለአቅመ ደካሞች የተገነቡ ስምንት መኖሪያ ቤቶች የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ሄለን ደበበ እና በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሐረሪ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙክታር ሳሊህ በተገኙበት ዛሬ ርክክብ ተካሂዷል።


በርክክብ ሥነ ስርዓቱ ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ሄለን ደበበ በለውጡ ዓመታት የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያጎለብት በርካታ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።


በተለይ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ የአቅመ ደካሞችና ሌሎች ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን ችግር በማቃለል ረገድ አበረታች ለውጥ ተገኝቶበታል ብለዋል።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ እርስ በርስ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህልን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ንጹህ መኖሪያ ቤትና ለኑሮ ምቹ አካባቢ እንዲያገኙ ማስቻሉን ተናግረዋል።


በዚህም ሚኒስቴሩ የበኩሉን ለመወጣት 20 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤቶችን በመገንባትና አስፈላጊውን ቁሳቁስ በማሟላት ማስረከቡን ገልጸዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙክታር ሳሊህ በወቅቱ እንዳሉት የክልሉ መንግስት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ሰፋፊ ሥራዎችን አከናውኗል።


በተለይ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አቅመ ደካማ ዜጎችን የመደገፍና የማገዝ ሥራዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው ሲከናወኑ መቆየታቸውን አንስተዋል።


ዛሬ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የተላለፉት ስምንት መኖሪያ ቤቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ በጥራትና በፍጥነት ተገንብተው መጠናቀቃቸውን ጠቁመው፣ በቀጣይም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎቹ ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

በመርሃ ግብሩ ከፌዴራል የመጡ ባለስልጣናትና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ ነዋሪዎችና ሌሎች እንግዶችም ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026