🔇Unmute
ሐረር፤ጥቅምት 16/2018 (ኢዜአ) ፡-የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከሐረሪ ክልል መንግስት ጋር በመተባበር በክልሉ ለአቅመ ደካሞች ያስገነባውን የመኖሪያ ቤት አጠናቆ አስረከበ።
በክልሉ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ለአቅመ ደካሞች የተገነቡ ስምንት መኖሪያ ቤቶች የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ሄለን ደበበ እና በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሐረሪ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙክታር ሳሊህ በተገኙበት ዛሬ ርክክብ ተካሂዷል።

በርክክብ ሥነ ስርዓቱ ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ሄለን ደበበ በለውጡ ዓመታት የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያጎለብት በርካታ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በተለይ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ የአቅመ ደካሞችና ሌሎች ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን ችግር በማቃለል ረገድ አበረታች ለውጥ ተገኝቶበታል ብለዋል።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ እርስ በርስ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህልን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ንጹህ መኖሪያ ቤትና ለኑሮ ምቹ አካባቢ እንዲያገኙ ማስቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም ሚኒስቴሩ የበኩሉን ለመወጣት 20 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤቶችን በመገንባትና አስፈላጊውን ቁሳቁስ በማሟላት ማስረከቡን ገልጸዋል።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙክታር ሳሊህ በወቅቱ እንዳሉት የክልሉ መንግስት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ሰፋፊ ሥራዎችን አከናውኗል።

በተለይ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አቅመ ደካማ ዜጎችን የመደገፍና የማገዝ ሥራዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው ሲከናወኑ መቆየታቸውን አንስተዋል።

ዛሬ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የተላለፉት ስምንት መኖሪያ ቤቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ በጥራትና በፍጥነት ተገንብተው መጠናቀቃቸውን ጠቁመው፣ በቀጣይም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎቹ ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
በመርሃ ግብሩ ከፌዴራል የመጡ ባለስልጣናትና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ ነዋሪዎችና ሌሎች እንግዶችም ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026