🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡-በሁሉም መስፈርት የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ስብራቶችን የጠገነበት ፍጥነትና ያስገኘው ውጤት አስደማሚ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ÷ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ያነገባቸውን ዓላማዎችና ያስገኛቸውን ውጤቶችን አብራርተዋል።
የሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የኢትዮጵያ የመጠባበቂያ ክምችት ከአስር ዕጥፍ በላይ ዕድገት እንዲያስመዘግብ ማስቻሉን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ ባለፈው በጀት ዓመት ትልቅ የሚባልና በዓለም ላይ በጣት ከሚቆጠሩ አራትና አምስት ሀገራት ባደጉበት የዕድገት ደረጃ ማደጓን አስረድተዋል።
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት በተሰራው ስራም በርካታ ኢንቨስተሮች ወደሀገር ቤት እየመጡ መሆኑን አንስተዋል።
የሀገር ውስጥ አልሚዎችም ሃብታቸውን በተቀናጀ መንገድ ኢትዮጵያ ውስጥ ማፍሰስ እንዲችሉ የተሰሩ ሰፋፊ ተግባራት ውጤት አምጥተዋል ነው ያሉት።
በሁሉም መስፈርት ሲታይ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ስብራቶችን የጠገነበት ፍጥነትና ያስገኘው ውጤት አስደማሚ ተብሎ የሚወሰድ መሆኑን አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025