🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡-በሁሉም መስፈርት የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ስብራቶችን የጠገነበት ፍጥነትና ያስገኘው ውጤት አስደማሚ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ÷ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ያነገባቸውን ዓላማዎችና ያስገኛቸውን ውጤቶችን አብራርተዋል።
የሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የኢትዮጵያ የመጠባበቂያ ክምችት ከአስር ዕጥፍ በላይ ዕድገት እንዲያስመዘግብ ማስቻሉን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ ባለፈው በጀት ዓመት ትልቅ የሚባልና በዓለም ላይ በጣት ከሚቆጠሩ አራትና አምስት ሀገራት ባደጉበት የዕድገት ደረጃ ማደጓን አስረድተዋል።
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት በተሰራው ስራም በርካታ ኢንቨስተሮች ወደሀገር ቤት እየመጡ መሆኑን አንስተዋል።
የሀገር ውስጥ አልሚዎችም ሃብታቸውን በተቀናጀ መንገድ ኢትዮጵያ ውስጥ ማፍሰስ እንዲችሉ የተሰሩ ሰፋፊ ተግባራት ውጤት አምጥተዋል ነው ያሉት።
በሁሉም መስፈርት ሲታይ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ስብራቶችን የጠገነበት ፍጥነትና ያስገኘው ውጤት አስደማሚ ተብሎ የሚወሰድ መሆኑን አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026