🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡-በሁሉም መስፈርት የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ስብራቶችን የጠገነበት ፍጥነትና ያስገኘው ውጤት አስደማሚ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ÷ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ያነገባቸውን ዓላማዎችና ያስገኛቸውን ውጤቶችን አብራርተዋል።
የሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የኢትዮጵያ የመጠባበቂያ ክምችት ከአስር ዕጥፍ በላይ ዕድገት እንዲያስመዘግብ ማስቻሉን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ ባለፈው በጀት ዓመት ትልቅ የሚባልና በዓለም ላይ በጣት ከሚቆጠሩ አራትና አምስት ሀገራት ባደጉበት የዕድገት ደረጃ ማደጓን አስረድተዋል።
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት በተሰራው ስራም በርካታ ኢንቨስተሮች ወደሀገር ቤት እየመጡ መሆኑን አንስተዋል።
የሀገር ውስጥ አልሚዎችም ሃብታቸውን በተቀናጀ መንገድ ኢትዮጵያ ውስጥ ማፍሰስ እንዲችሉ የተሰሩ ሰፋፊ ተግባራት ውጤት አምጥተዋል ነው ያሉት።
በሁሉም መስፈርት ሲታይ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ስብራቶችን የጠገነበት ፍጥነትና ያስገኘው ውጤት አስደማሚ ተብሎ የሚወሰድ መሆኑን አስረድተዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026