የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የግብርና ምርምር ማዕከላት ግብርናን በማዘመን ለዘርፉ ውጤታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ አድርገዋል - ቢሮው

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ወራቤ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ምርምር ማዕከላት ግብርናን በማዘመን ለዘርፉ ውጤታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል ለስርዓተ ምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም በዘር ብዜት፣ በምርምርና በቴክኖሎጂ ሽግግር ባከናወናቸው ተግባራት ላይ የመስክ ምልከታ ተካሂዷል።

የቢሮው ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ ዓለምይርጋ ወልደስላሴ በዚህ ወቅት እንዳሉት በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና ምርምር ማዕከላት ተጨማሪ አቅም እየሆኑን ነው።

በግብርና ዘርፍ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በራስ አቅም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ከተረጂነት ለመወጣት እየተደረገ ባለው ጥረት ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል።

በሌማት ትሩፋት፣ በአረንጓዴ ዐሻራና በሌሎች የግብርና ሥራዎችም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት በማሳደግ በኩል ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ነው የጠቆሙት።

ባለፈው ዓመት በክልሉ በበልግ፣ በመኸርና በበጋ መስኖ ልማት 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር ማሳ በማልማት 142 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ገልጸዋል።

ለዚህም የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርጥ ዘር ብዜት፣ የተሻሻሉና በምርምር የተደገፉ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅና በማሸጋገር ያበረከተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አስታውሰዋል።

በዚህ ዓመትም 159 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ግብ ተጥሎ ወደ ተግባር መገባቱን ነው ምክትል ቢሮ ኃላፊው የተናገሩት።

የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ጌታሁን ያዕቆብ(ዶ/ር) በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ የግብርና ልማት ሥራውን የሚያግዙ ተግባራት በማከናወን ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

የሀገራዊና ክልላዊ ኢንሼቲቮች ትግበራን በምርምርና በቴክኖሎጂ እያገዘ እንደሚገኝም ነው የገለጹት።

የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ቀድራላ ዋበላ(ዶ/ር) እንዳሉት ማዕከሉ ግብርናን ማዘመን የሚያስችል የምርምር፣ የዘር ብዜትና ቴክኖሎጂን የማስተዋወቅ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

በዚህም የአካባቢን ስነ ምህዳር መሰረት በማድረግ የዘር ብዜት፣ የሰብል ጥበቃና እንስሳት ዝርያ ማሻሻልን ጨምሮ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በመስክ ምልከታው የክልሉ ግብርና ቢሮ፣ የምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ አመራሮችና አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026