የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የባህር በር ጥያቄን ማንሳት እንደ ጥፋት ይቆጠር የነበረበት ጊዜ አብቅቶ አሁን የመብት ጥያቄ መነሳቱ ተገቢና ምላሽ ማግኘት ያለበት ጉዳይ ነው

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ የባህር በር ጥያቄን ማንሳት እንደ ጥፋት ይቆጠር የነበረበት ጊዜ አብቅቶ አሁን የመብት ጥያቄ መነሳቱ ተገቢና ምላሽ ማግኘት ያለበት ጉዳይ መሆኑን ምሁራን ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ ለምክር ቤት አባላት ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ህጋዊ፣ ታሪካዊና መልክዓ ምድራዊ መብት የነበራት ብትሆንም ለምን እና በማን ውሳኔ እንዳጣች እስካሁን መረጃና ማስረጃ ማግኘት አለመቻሉን መግለጻቸው ይታወሳል።

በመሆኑም ከባህር ልትገለልና የባህር በር ልታጣ አይገባም በማለት መንግስት የባህር በር ጉዳይን የህልውና ጉዳይ አድርጎ ጥረቱን አጠናክሮ ቀጥሏል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የታሪክ መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ እና በአውስትራሊያ የናሽናል ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ዳንኤል መኮንን፤ የባህር በር ጥያቄን ማንሳት እንደ ጥፋት ይቆጠር የነበረበት ጊዜ አብቅቶ የመብት ጥያቄ መነሳቱ ተገቢና ምላሽ ማግኘት ያለበት ጉዳይ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ባህር አካሏ የባህር በር ደግሞ የእድገትና ህልውናዋ መሰረት እንደነበር የሚያስታውሱት ፕሮፌሰር አየለ በክሪ፤ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በመንፈግ የባህር በር ለምን አጣች የሚለው ጉዳይ ዜጎችን እያስቆጨ ያለ መሆኑን አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ ቀይ ባህር ላይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ መብት ያላት መሆኑን መግለፃቸው ተገቢና ትክክለኛ ነው ብለዋል።

ከዚህ በፊት የባህር በር ጥያቄን ማንሳት እንደ ጥፋት ይቆጠር የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ በቁጭት መንግስት የሀገር የህልውና ጉዳይ አድርጎ መያዙን አድንቀው የኢትዮጵያ ህጋዊ፣ ታሪካዊና መልክዓ ምድራዊ የባህር በር ባለቤትነት መብቷ ምላሽ ሊያገኝ እንደሚገባ በአጽንኦት ሰጥተዋል።

በዚህ ጉዳይ ላይ የመንግስት ጥረት እንዳለ ሆኖ ከቀይ ባህር በቅርብ ርቀት ላይ ሆነን በተዘጋ ሀገር ውስጥ መኖር የሌለብን በመሆኑ ሁላችንም ለመብትና ተጠቃሚነታችን በጋራ መቆም አለብን ብለዋል።

በአውስትራሊያ ናሽናል ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ዳንኤል መኮንን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ መንግስት የያዘው ጠንካራ አቋም የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል።

በመሆኑም ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ነባራዊ ሁኔታ፣ ካላት የህዝብ ቁጥር እና ግዙፍ የኢኮኖሚ ዕድገት አንፃር የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ያለበት ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለምክር ቤት አባላት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑ ማንሳታቸው ይታወሳል።

ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት ምክንያትም በማን እንደተወሰነ የሚያመላክት አንዳችም ማስረጃ እንደሌለ ጨምረው ማስረዳታቸው እንዲሁ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026