🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 22/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በታዳሸ ሀይል እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት የኢንዱስትሪ ምርቶቿን ደረጃ ከፍ በማድረግ በአውሮፓ ገበያ ተወዳዳሪነቷን ማሳደግ እንደሚያስችላት በኢትዮጵያ የጀርመን ተጠባባቂ አምባሳደር ፈርዲናንድ ቮን ዌይ ገለጹ።
ተጠባባቂ አምባሳደሩ እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያ በኢኮኖሚው ዘርፍ እየተደረጉ ያሉ ማሻሻያዎች የሚበረታቱ ናቸው።
እነዚህ ስራዎችም ከዲጂታላይዜሽን እና ፈጠራ ጋር ተያይዘው የሚሄዱ መሆናቸውን አመልክተዋል።
በሀገሪቱ እየተከናወኑ ያሉ የኢኮኖሚ ለውጦች ለወጣቶች፣ ለፈጠራ ባለሙያዎች ሃሳባቸውን በትክክል ወደ ተግባር መለወጥ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ለታዳሽ ኃይል የሰጠችው ትኩረት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው የውሃ፣ የንፋስ፣ የጂኦተርማል እና የፀሐይ ኃይል አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ በታዳሸ ሀይል እያከናወነቻቸው ያሉ ስራዎች የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ምርቶች ተወዳዳሪነት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድገው ተናግረዋል።
ከእነዚህ የሀይል ምንጮች የሚወጡ ምርቶች በአውሮፓ ገበያ ላይም ተወዳዳሪነታቸውን እንደሚጨምር ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ እና ጀርመን በርካታ ዓመታት ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዳላቸው አመልክተው፤ የሁለቱ ሀገራት መንግስታት በበርካታ ጉዳዮች ላይ በጋራ እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።
የግብርና እና የገጠር ልማት ስራዎች ለዚህ ተጠቃሽ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በሀገራቱ መካከል ትልቅ ትብብር እና መተማመን መኖሩን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026