🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 22/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በታዳሸ ሀይል እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት የኢንዱስትሪ ምርቶቿን ደረጃ ከፍ በማድረግ በአውሮፓ ገበያ ተወዳዳሪነቷን ማሳደግ እንደሚያስችላት በኢትዮጵያ የጀርመን ተጠባባቂ አምባሳደር ፈርዲናንድ ቮን ዌይ ገለጹ።
ተጠባባቂ አምባሳደሩ እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያ በኢኮኖሚው ዘርፍ እየተደረጉ ያሉ ማሻሻያዎች የሚበረታቱ ናቸው።
እነዚህ ስራዎችም ከዲጂታላይዜሽን እና ፈጠራ ጋር ተያይዘው የሚሄዱ መሆናቸውን አመልክተዋል።
በሀገሪቱ እየተከናወኑ ያሉ የኢኮኖሚ ለውጦች ለወጣቶች፣ ለፈጠራ ባለሙያዎች ሃሳባቸውን በትክክል ወደ ተግባር መለወጥ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ለታዳሽ ኃይል የሰጠችው ትኩረት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው የውሃ፣ የንፋስ፣ የጂኦተርማል እና የፀሐይ ኃይል አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ በታዳሸ ሀይል እያከናወነቻቸው ያሉ ስራዎች የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ምርቶች ተወዳዳሪነት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድገው ተናግረዋል።
ከእነዚህ የሀይል ምንጮች የሚወጡ ምርቶች በአውሮፓ ገበያ ላይም ተወዳዳሪነታቸውን እንደሚጨምር ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ እና ጀርመን በርካታ ዓመታት ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዳላቸው አመልክተው፤ የሁለቱ ሀገራት መንግስታት በበርካታ ጉዳዮች ላይ በጋራ እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።
የግብርና እና የገጠር ልማት ስራዎች ለዚህ ተጠቃሽ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በሀገራቱ መካከል ትልቅ ትብብር እና መተማመን መኖሩን ተናግረዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026