የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኢትዮጵያ የተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን የማንሰራራት ጉዞ የሚያረጋግጡ ናቸው-ምሁራን

Nov 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ጥቅምት 22/2018 (ኢዜአ) ፡- የተጀመሩ ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ እውን ለማድረግ ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን የዋቸሞ ዩኒቨርሰቲ ምሁራን ገለፁ።

የዘመናት ቁጭት የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በተጠናቀቀ ማግስት በሶማሌ ክልል ካሉብ በዓመት 111 ሚሊዮን ሊትር ማምረት የሚችለውን የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ ተመርቆ የሁለተኛ ዙር ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ መጀመሩ የሚታወስ ነው።

መንግስት በበጀት ዓመቱ የኒኩሌር ፕላንት፣ የማዳበሪያ ፋብሪካ፣ የነዳጅ ማጣሪያ፣ ግዙፍ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አየር ማረፊያን ጨምሮ ሜጋ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጀመሩ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

እነዚህ የልማት ፕሮጀክቶች ለሀገራዊ እድገት መፋጠን ያላቸውን ፋይዳ በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን የተጀመሩ ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ እውን ለማድረግ ጉልህ ጠቀሜታ ያላቸው ናቸው።

በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህር ጌታሁን አበራ ኢትዮጵያውያን ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በራሳቸው አቅም መገንባት እንደሚችሉ በሕዳሴው ግድብ ማሳየታቸውን አስታውሰዋል።

ይህም ሌሎች ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ማሳካት እንደሚቻል ጥሩ ማሳያ መሆኑን ገልጸው፣ መንግስት በቅርቡ ይፋ ያደረጋቸው ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞ አይቀሬ መሆኑን የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል።

እየታየ ያለው ሁለንተናዊ የዕድገት ጉዞና የተጀመሩ የልማት ዕቅዶች ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ከመመለስ ባለፈ የመደራደር እና የተደማጭነት አቅሟን እንደሚያሳድገውም መምህር ጌታሁን አንስተዋል፡፡

ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ጸጋዎች የተቸረች ብትሆንም ጸጋዎችን በራስ አቅም አልምታ መጠቀም ላይ ችግሮች እንደነበሩ አስታውሰዋል።

ለዚህም የውጭና የውስጥ ተጽዕኖ እና ለልማት ቁርጠኛ አለመሆናችንን እንደእንድ ምክንያት የጠቀሱት መምህሩ፣ በአሁኑ ወቅት መንግስት ሀገርን ለማልማት ያለውን ጽኑ ፍላጎት በተግባር እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።

በቅርቡ የተጀመሩና የሀገርን የማንሰራራት ጉዞ የሚያረጋግጡ ሜጋ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ዜጎች በገንዘብ፣ በሀሳብና ሰላምን በማጽናት ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸውም ገልጸዋል።

በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ሙሉአለም ኃይለማርያም በበኩላቸው መንግስት በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ለማመን የሚከብዱ ታላላቅ የልማት ሥራዎችን ማከናወኑን አድንቀዋል፡፡

በተለይ በቅርቡ ያስጀመራቸው ሜጋ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ የኢትዮጵያን የቀጣይ እጣ ፈንታ የሚወስኑ፣ የተሻለ የሚያደርጉና ዓለም አቀፍ ተሰሚነቷን የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል።

የልማት ፕሮጀክቶቹን ለስኬት በማብቃት እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ጋር በማስተሳሰር የዜጎችን ተጠቃሚነት ወደላቀ ደረጃ ማሳደግ እንደሚቻል ገልጸው፣ ፕሮጀክቶቹ የሀገርን የመደራደር አቅም ከፍ ያደርጋሉ ብለዋል።

እንደ መምህር ሙሉአለም ገለጻ ፕሮጀክቶቹ በታሰበው የጊዜ ገደብ ተጠናቅቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ በሕዳሴው ግድብ የታየው አንድነትና ትብብር ሊጠናክር ይገባል።

በሀገር ልማትና ብሔራዊ ጥቅም ልዩነት ሊኖረን አይገባም ያሉት መምህሩ፣ ለዚህም ከመንግስት ጋር ተቀናጅቶና ተባብሮ መስራት እንደሚገባ ነው የገለጹት።

በተለይ ውስጣዊ አንድነትን ማጠናከር የዚህ ትውልድ አደራ መሆን እንዳለበት ነው ያስገነዘቡት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025