🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 22/2018(ኢዜአ)፦ የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤን በመለወጥ የተሟላ ብልጽግና ማረጋገጥን ያለመ መሆኑን የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ።
ሙሉ መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል፦
መንግሥት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማን ለመገንባት የኮሪደር ልማቱን ከአዲስ አበባ በመጀመር ሁሉም ክልሎች ላይ ከተሞችን የማልማት ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡ ይህ የኮሪደር ልማቱ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ከማረጋገጥ አኴያ የጎላ ሚና አለዉ፡፡ ሌሎች ከተሞችም አዲስ አበባ ከኮሪደር ልማት በፊት ምን እንደምትመስል፤ ልማቱ ሲሰራ የነበረዉን ሁኔታ እና የኮሪደር ልማቱ ካለቀ በኃላ ያለዉን ለዉጥ የሚያሳይ ልምድ ከወሰዱ በኃለ በመላዉ ኢትዮጵያ 68 ከተሞች ላይ የኮሪደር ልምት መስራት ተችሏል፡፡
የኮሪደር ልማቱ ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሳሳረ ልማት ሲሆን፤ ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሓዊ ልማት ለዜጎቻችን ለማቅረብ በማለም ለሌሎች ሀገራት ምሳሌ ሊሆን በሚችል መልኩ ከተሞች እያለሙ ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ግን ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚኖረዉ ገጠር በማሆኑ የዜጎችን ህይወት ለመቀየር እና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በከተማ የተሰራ የኮሪደር ልማት በቂ አይደለም፡፡ በከተሞች የታየዉን አመርቂ ዉጤት በገጠርም መታየት አለበት።
ስለዚህ የኮሪደር ልማቱ በከተማ ብቻ ሳይገደብ የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗርን ለማሻሻል የገጠር ኮሪደር ልማት ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2017 ግንቦት ወር መጨረሻ የገጠር ኮሪደር ልማት አካል የሆነውን ሞዴል የገጠር መንደሮች ግንባታ ማስጀመራቸው ይታወሳል። የተሻላ ኖሮን ፍለጋ ከከተማ ወደ ገጠር የሚደረገዉን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገትን ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት ተግባራዊ ማድረግ ወሳኝ ነዉ፡፡ ይህ ደግሞ የተስተካከለ ኑሮን እና ከተሜነትን ወደ ገጠር በማምጣት፤ ሞዴል የገጠር መንደሮቹ ቀላል ወጪ የሚጠይቁና በአካባቢው በሚገኙ ግብዓቶች የሚገነቡ፤ እንዲሁም አርሶ አደሩ ጤናማ እና ክብር ያለውን ህይወት እንዲኖር የሚያስችል የልማት አካል ነዉ። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ስነ ምህዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ሲሆን ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽዖ አለው።
ከለዉጡ በፊት የኢኮኖሚ ምንጭ የሆነው የገጠሩ አካባቢ ትኩረት ተነፍጎት የቆያ ሲሆን፤ የተሻለ ኑሮን ፍለጋ ወደ ከተማ የሚሄደውን አርሶ አደር በሚኖርበት ተረጋግቶ እሴት መጨመር ላይ እየሰራ እንዲኖር የሚያስችል ሁኔታ ነዉ የለውጡ መንግሥት የፈጠረዉ። የገጠር ኮሪደር አጠቃላይ የኅብረተሰብ ሽግግርን የሚያመጣ እና መሰረተ ልማትን ጨምሮ የተለያዩ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ጉዳዮችን ያቀፈ ሲሆን፤ በገጠር አካባቢዎች ዘመናዊ አኗኗርን የሚፈጥር እና የአርሶ አደሩን ህይወት የሚቀይር ይሆናል።
በአጠቃላይ የገጠር ኮሪደር ልማት አርሶ አደሩ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚና ዘመናዊ ስልተ-ምርት እንዲከተል የምየደርግ ሲሆን አርሶ አደሩ ባህሉንና ወጉን ጠብቆ አካባቢውን ንጹህ፣ ጓሮውን በዶሮ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ እንዲሁም በማርና ወተት ምርት የተትረፈረፈ በማድረግ ቀላል የአኗኗር ስልት እንዲከተል ያደርጋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025