የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የምሽት ንግድ የሥራ ባህልን በማሳደግ የተሻለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ፈጥሯል  

Nov 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 23/2018 (ኢዜአ):-የአዲስ አበባ ከተማ የምሽት ንግድ የአሰራር ሥርዓት የሥራ ባህልን በማሳደግ የተሻለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መፍጠሩን የከተማ አስተዳደሩ ንግድ ቢሮ ገለጸ።

በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች የነዋሪዎችን የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ በማሳለጥ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያሻሻለ ይገኛል።

በዚህም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በደንብ ቁጥር 185/2017 የንግድና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እስከ ምሽት 3:30 አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው የሚደነግግ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል።

በመዲናዋ የተፈጠረው የምሽት ንግድና አገልግሎት የአሰራር ሥርዓትም በዘርፉ የተሰማሩ ዜጎችን የሥራ ባህል በማሻሻል ኢኮኖሚያዊ ገቢን እያሻሻለ እንደሚገኝ ይገለፃል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የንግድ ቢሮና ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስራ ኃላፊዎችም የመዲናዋን የምሽት ንግድና አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ተዘዋውረው ምልከታ አድርገዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ የንግድ ሬጉላቶሪ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ስመኘው ተሾመ፥ በመዲናዋ የምሽት ንግድ አሰራር ሥርዓቶችን ባህል ማድረግ የሚያስችል ምቹ የመሠረተ ልማት ምኅዳር ተፈጥሯል ብለዋል።


የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት የምሽት ንግድና አገልግሎት ደንብም የመዲናዋን የዲፕሎማቲክ ማዕከልነት የሚመጥን የምሽት ንግድና አገልግሎት ባህል እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።

የመዲናዋ የኮሪደር ልማት የፈጠረው የምሽት ንግድ ባህልም የንግድ ሥርዓቱን በማዘመን በልምድና አርዓያነት የሚወሰድ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንዲፈጠር ማድረጉን ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ ጸጋዬ ደበሌ÷ የኮሪደር ልማት ለምሽት ንግድ የፈጠረው ዕድል የአገልጋዮችንና ተገልጋዮችን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው ብለዋል።


በመዲናዋ በንግድና አገልግሎት የተሰማሩ ተቋማት የከተማ አስተዳደሩን የምሽት ንግድና አገልግሎት ደንብ ተከትለው እንዲሰሩም ቀጣይነት ያለው ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የምሽት ንግድ የአሰራር ሥርዓቱ በመዲናዋ ኢኮኖሚያዊ መነቃቃትን ፈጥሯል ያሉት ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ ከፍያለው ታደሰ ናቸው።


የመዲናዋን ንግድና አገልግሎት ለማሳለጥም እስከ ብሎክ አደረጃጀት ድረስ ከጸጥታ አካላት ጋር የተቀናጀ የድጋፍና ክትትል ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢዜአ ካነጋገራቸው ነጋዴዎች መካከል አስቴር ይታየው÷ የኮሪደር ልማት ለምሽት አገልግሎት ሰጪ ሱቆች የተለየ ውበት በማላበስ የህብረተሰቡን የግብይት ባህል እያሳደገ ነው ብለዋል።


ወጣት አብዱረዛቅ ኑር-ሁሴን በበኩሉ÷ የመዲናዋን የኮሪደር ልማት ተከትሎ ተግባራዊ የተደረገው የምሽት ንግድ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደገ እንደሚገኝ ገልጿል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026