🔇Unmute
ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በበጀት አመቱ ሶስት ወራት በህገ-ወጥ ንግድ የተሰማሩ ከ49 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ንግድ ቢሮ ምክትል ሀላፊ ተስፋዬ ገሾ ለኢዜአ እንደተናገሩት በክልሉ ህገ-ወጥ የንግድ ተግባራትን በመከላከል ጤናማ የንግድ ስርዓትን ለማስፈን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው።
በበጀት አመቱ ባለፉት ሶስት ወራት ከክልሉ ፖሊስ፣ ከዐቃቤ ህግ፤ ከገቢዎችና ከትራንስፖርት ቢሮዎች የተውጣጣ ግብረ ሀይል ተቋቁሞ በየዞኑና በከተሞች ሰፊ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም በተሰጠው የግንዛቤ ፈጠራ ህብረተሰቡ የህገ-ወጥ ንግድ ስራ ላይ የሚያጋጥመውን ወንጀል በማሳወቅና ጥቆማ በመስጠት ከፍተኛ ሚና እንደነበረው ተናግረዋል።
በክልሉ ያለ ንግድ ፈቃድ ንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ፤ ምርትን ከባዕድ ነገሮች ጋር ቀላቅሎ መሸጥ፤ የዋጋ ዝርዝር ያለመለጠፍ የመሳሰሉ ህገወጥ ተግባራት በፈጸሙ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።
በተጨማሪም ሚዛን የሚያጭበረብሩ፤ ደረሰኝ የማይሰጡ፤ ያለአግባብ ምርትንና ሸቀጦችን የሚያከማቹ እና የሚደብቁ የንግድ ተቋማት ላይ ማስጠንቀቂያ የመስጠት፣ የማሸግና ሌሎች አስተዳደራዊ እርምጃዎች ተወስዷል ነው ያሉት።
በተለይም በነዳጅ ህገ ወጥ ንግድ ላይ የተሰማሩ 30 ግለሰቦች በህግ ተጠያቂ የሆኑ ሲሆን ከዚህ ውስጥ አምስት ሰዎች በ4 አመት እስር እንዲቀጡ መደረጉን ተናግረዋል።
ቢሮው ህገ-ወጥ ንግድ ላይ የተሰማሩ አካላትን ወደ ህጋዊ መስመር እንዲመለሱ የማድረጉንና ጤናማ የንግድ ስርዓት ላይ ያሉትን ደግሞ የማበረታታት ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026