የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ ባለፉት ሶስት ወራት በህገ-ወጥ ንግድ በተሰማሩ ከ49ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወስዷል - የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ

Nov 6, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በበጀት አመቱ ሶስት ወራት በህገ-ወጥ ንግድ የተሰማሩ ከ49 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ንግድ ቢሮ ምክትል ሀላፊ ተስፋዬ ገሾ ለኢዜአ እንደተናገሩት በክልሉ ህገ-ወጥ የንግድ ተግባራትን በመከላከል ጤናማ የንግድ ስርዓትን ለማስፈን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው።

በበጀት አመቱ ባለፉት ሶስት ወራት ከክልሉ ፖሊስ፣ ከዐቃቤ ህግ፤ ከገቢዎችና ከትራንስፖርት ቢሮዎች የተውጣጣ ግብረ ሀይል ተቋቁሞ በየዞኑና በከተሞች ሰፊ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም በተሰጠው የግንዛቤ ፈጠራ ህብረተሰቡ የህገ-ወጥ ንግድ ስራ ላይ የሚያጋጥመውን ወንጀል በማሳወቅና ጥቆማ በመስጠት ከፍተኛ ሚና እንደነበረው ተናግረዋል።

በክልሉ ያለ ንግድ ፈቃድ ንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ፤ ምርትን ከባዕድ ነገሮች ጋር ቀላቅሎ መሸጥ፤ የዋጋ ዝርዝር ያለመለጠፍ የመሳሰሉ ህገወጥ ተግባራት በፈጸሙ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።

በተጨማሪም ሚዛን የሚያጭበረብሩ፤ ደረሰኝ የማይሰጡ፤ ያለአግባብ ምርትንና ሸቀጦችን የሚያከማቹ እና የሚደብቁ የንግድ ተቋማት ላይ ማስጠንቀቂያ የመስጠት፣ የማሸግና ሌሎች አስተዳደራዊ እርምጃዎች ተወስዷል ነው ያሉት።

በተለይም በነዳጅ ህገ ወጥ ንግድ ላይ የተሰማሩ 30 ግለሰቦች በህግ ተጠያቂ የሆኑ ሲሆን ከዚህ ውስጥ አምስት ሰዎች በ4 አመት እስር እንዲቀጡ መደረጉን ተናግረዋል።

ቢሮው ህገ-ወጥ ንግድ ላይ የተሰማሩ አካላትን ወደ ህጋዊ መስመር እንዲመለሱ የማድረጉንና ጤናማ የንግድ ስርዓት ላይ ያሉትን ደግሞ የማበረታታት ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026