የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የሕዳሴ ግድብ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ ለዲጂታላይዜሽን መሻሻል ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረክታል

Nov 6, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለማሻሻል ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው ተቋማት ገለፁ።

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለሁለንተናዊ ማክሮ ኢኮኖሚ እድገትና የፋይናንስ አካታችነትን ለማረጋገጥ አስተዋፅኦ እንዳለውም ገልጸዋል።

የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ቢዝነስ ኦፊሰር ብሩክ አድሃና ለኢዜአ እንዳሉት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከዓድዋ ድል በኋላ የአፍሪካ የነፃነት ተምሳሌትነታችንን የደገምንበት ፕሮጀክት ነው።

የሕዳሴ ግድቡ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ ለዲጂታላይዜሽን መፋጠን ካለው ፋይዳ በተጨማሪ ለሁለንተናዊ የማክሮ ኢኮኖሚ እድገት ጉልህ አስተዋፅኦ አለው ብለዋል።

ግድቡ የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን በማሳደግ ለመሰረተ ልማት መስፋፋትና ለሁለንተናዊ የህብረተሰብ እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

ዘላቂ የኃይል አቅርቦት የኔትወርክ ጥራትን ለማረጋገጥና የፋይናንስ አካታችነትን ተደራሽ ለማድረግ ሚና እንዳለው አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ ሳፊ ገመዲ በበኩላቸው፤ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያዊያን በጋራ የፈፀምነው ዳግማዊ ዓድዋ ነው ብለዋል።

አገልግሎቱ በሀገሪቱ ተአማኒና ወቅታዊ መረጃ የሚያቀርብ መሆኑን ጠቁመው፣ የተቋሙ 26 ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች የራሳቸው ሰርቨር ያላቸውና ግዙፍ የኃይል አቅርቦት የሚፈልጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ግድቡ ዘላቂ የኃይል አቅርቦትን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተከትሎ አገልግሎቱ የተሳለጠ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዘመናዊ የስታትስቲክስ ስርዓት ለመገንባት ለጀመረው ጥረት አስተዋፅኦ እንዳለው ገልፀዋል።

አገልግሎቱ ግድቡ የሚያመነጨውን ሃይል ለዲጂታል ቴክኖለጂ በመጠቀም የሚሰበስበውን መረጃ ጥራት ለማስጠበቅና መረጃ አሰባሰቡን የተሳለጠ ለማድረግ እንደሚያስችለው ነው ያስረዱት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026