🔇Unmute
ሀዋሳ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ በሀዋሳ ከተማ የሚገኙ የቱሪስት መስህቦችን በማልማት ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ተክሌ ጆንባ አስታወቁ።
ሀዋሳ ከተማ የፍቅር ሀይቅ፣ ታቦርና አላሙራ ተራራን የመሳሰሉ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን በውስጧ ይዛለች።
ከተፈጥሯዊ መስህቦቿ ባለፈ ባህላዊና ሀይማኖታዊ በዓላት የሚከበሩባት መሆኗ በጎብኚዎች ተመራጭ አድርጓታል ።

ይህን የከተማዋን ቱሪስት መስህብነት የኮሪደር ልማትና ሌሎች የጉብኝት መዳረሻዎች ልማት እያሳደገው ነው።
ለአብነትም የታቦር ተራራን ለመዝናኛና ለአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምቹ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ተጠናቀው በቅርቡ በከፊል ክፍት ተደርገዋል።
የከተማዋ ከንቲባ አቶ ተክሌ ጆንባ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የተለያዩ የልማት ስራዎችን በመስራት ሀዋሳ ከተማን ለጎብኚዎች ተመራጭ ማድረግ ተችሏል።
የከተማዋን የኮሪደር ልማት ግንባታና የታቦር ተራራን በማልማት ምቹ በማድረግ የጎብኚዎችን ቁጥር በመጨመር የዘርፉን ገቢ ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በታቦር ተራራ ላይ የእረፍት ጊዜያቸውን በመዝናናት ሲያሳልፉ ያገኘናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች እንዳሉት የታቦር ተራራ መዝናኛ ስፍራ ልማት ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ከሚያበረክተው አስተዋጽኦ ባለፈ ለስፖርት እንቅስቃሴ የጎላ ድርሻ አለው።

ነዋሪዎቹ ታቦር ተራራ ለሀዋሳ ከተማ ልዩ ውበት መሆኑን ገልፀው የተጀመረው ፕሮጀክት ተጠናቆ ለጎብኚዎች ክፍት በመደረጉ መደሰታቸውን ገልፀዋል።

የታቦር ተራራ ልማት ለከተማዋ ነዋሪዎች ተጨማሪ የመዝናኛ ስፍራን መፍጠሩንም ነው የተናገሩት።
ስፍራውንም በማስፋፋት ለከተማዋ ገቢ የድርሻውን እንዲወጣ ማድረግ እንደሚገባም አመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025