የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በሀዋሳ ከተማ የሚገኙ የመስህብ ስፍራዎችን በማልማት ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ  እየተሰራ ነው

Nov 7, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ በሀዋሳ ከተማ የሚገኙ የቱሪስት መስህቦችን በማልማት ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ተክሌ ጆንባ አስታወቁ።

ሀዋሳ ከተማ የፍቅር ሀይቅ፣ ታቦርና አላሙራ ተራራን የመሳሰሉ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን በውስጧ ይዛለች።

ከተፈጥሯዊ መስህቦቿ ባለፈ ባህላዊና ሀይማኖታዊ በዓላት የሚከበሩባት መሆኗ በጎብኚዎች ተመራጭ አድርጓታል ።


ይህን የከተማዋን ቱሪስት መስህብነት የኮሪደር ልማትና ሌሎች የጉብኝት መዳረሻዎች ልማት እያሳደገው ነው።

ለአብነትም የታቦር ተራራን ለመዝናኛና ለአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምቹ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ተጠናቀው በቅርቡ በከፊል ክፍት ተደርገዋል።

የከተማዋ ከንቲባ አቶ ተክሌ ጆንባ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የተለያዩ የልማት ስራዎችን በመስራት ሀዋሳ ከተማን ለጎብኚዎች ተመራጭ ማድረግ ተችሏል።

የከተማዋን የኮሪደር ልማት ግንባታና የታቦር ተራራን በማልማት ምቹ በማድረግ የጎብኚዎችን ቁጥር በመጨመር የዘርፉን ገቢ ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።


በታቦር ተራራ ላይ የእረፍት ጊዜያቸውን በመዝናናት ሲያሳልፉ ያገኘናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች እንዳሉት የታቦር ተራራ መዝናኛ ስፍራ ልማት ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ከሚያበረክተው አስተዋጽኦ ባለፈ ለስፖርት እንቅስቃሴ የጎላ ድርሻ አለው።


ነዋሪዎቹ ታቦር ተራራ ለሀዋሳ ከተማ ልዩ ውበት መሆኑን ገልፀው የተጀመረው ፕሮጀክት ተጠናቆ ለጎብኚዎች ክፍት በመደረጉ መደሰታቸውን ገልፀዋል።


የታቦር ተራራ ልማት ለከተማዋ ነዋሪዎች ተጨማሪ የመዝናኛ ስፍራን መፍጠሩንም ነው የተናገሩት።

ስፍራውንም በማስፋፋት ለከተማዋ ገቢ የድርሻውን እንዲወጣ ማድረግ እንደሚገባም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026