የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በሀዋሳ ከተማ የሚገኙ የመስህብ ስፍራዎችን በማልማት ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ  እየተሰራ ነው

Nov 7, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ በሀዋሳ ከተማ የሚገኙ የቱሪስት መስህቦችን በማልማት ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ተክሌ ጆንባ አስታወቁ።

ሀዋሳ ከተማ የፍቅር ሀይቅ፣ ታቦርና አላሙራ ተራራን የመሳሰሉ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን በውስጧ ይዛለች።

ከተፈጥሯዊ መስህቦቿ ባለፈ ባህላዊና ሀይማኖታዊ በዓላት የሚከበሩባት መሆኗ በጎብኚዎች ተመራጭ አድርጓታል ።


ይህን የከተማዋን ቱሪስት መስህብነት የኮሪደር ልማትና ሌሎች የጉብኝት መዳረሻዎች ልማት እያሳደገው ነው።

ለአብነትም የታቦር ተራራን ለመዝናኛና ለአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምቹ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ተጠናቀው በቅርቡ በከፊል ክፍት ተደርገዋል።

የከተማዋ ከንቲባ አቶ ተክሌ ጆንባ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የተለያዩ የልማት ስራዎችን በመስራት ሀዋሳ ከተማን ለጎብኚዎች ተመራጭ ማድረግ ተችሏል።

የከተማዋን የኮሪደር ልማት ግንባታና የታቦር ተራራን በማልማት ምቹ በማድረግ የጎብኚዎችን ቁጥር በመጨመር የዘርፉን ገቢ ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።


በታቦር ተራራ ላይ የእረፍት ጊዜያቸውን በመዝናናት ሲያሳልፉ ያገኘናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች እንዳሉት የታቦር ተራራ መዝናኛ ስፍራ ልማት ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ከሚያበረክተው አስተዋጽኦ ባለፈ ለስፖርት እንቅስቃሴ የጎላ ድርሻ አለው።


ነዋሪዎቹ ታቦር ተራራ ለሀዋሳ ከተማ ልዩ ውበት መሆኑን ገልፀው የተጀመረው ፕሮጀክት ተጠናቆ ለጎብኚዎች ክፍት በመደረጉ መደሰታቸውን ገልፀዋል።


የታቦር ተራራ ልማት ለከተማዋ ነዋሪዎች ተጨማሪ የመዝናኛ ስፍራን መፍጠሩንም ነው የተናገሩት።

ስፍራውንም በማስፋፋት ለከተማዋ ገቢ የድርሻውን እንዲወጣ ማድረግ እንደሚገባም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026