🔇Unmute
ወላይታ ስዶ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ መናኸሪያ የተጀመረው በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር ከእንግልት እና አግባብ ካልሆነ የታሪፍ ክፍያ ታድጎናል ሲሉ የመናኸሪያው ተገልጋዮች ተናገሩ።
በወላይታ ሶዶ ከተማ የተጀመረው የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት ዙሪያ ኢዜአ ተገልጋዮችን አነጋግሯል።
ተገልጋዮቹ እንዳሉት፤ በከተማዋ መናኸሪያ የተጀመረው በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር ከዚህ ቀደም ይገጥማቸው የነበረን ከታሪፍ በላይ የመክፈልና አላስፈላጊ እንግልት አስቀርቶላቸዋል።
አቶ ብሩክ ዘውዴ ከዚህ ቀደም የትራንስፖርት አገልግሎቱ ካለመዘመኑ የተነሳ ለተለያዩ ችግሮች ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል።
በቴክኖሎጂ የተደገፈ የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህ ያለአግባብ ይደርስብን የነበረው እንግልትና የታሪፍ በላይ ክፍያ ከማስቀረት ባሻገር ጊዜያችንን ቆጥቦልናል ብለዋል።
ሌላኛዋ ተገልጋይ ወይዘሮ የእናትፋንታ ኢያሱ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም ትክክለኛውን ታሪፍ እንኳን ለማወቅ ይቸገሩ እንደነበር አስታውሰው የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት በርካታ መረጃዎችን መዝግቦ በመያዙ ሳይጨናነቁ እና ትርፍ ሳይከፍሉ መገልገል መጀመራቸውን ገልጸዋል።
ተሽከርካሪዎችም ትርፍ መጫን ስለማይችሉ እና ወጪ ወራጅ ስለማይበዛ ወዳሰብንበት ቦታ በጊዜ እንድንደርስ ከማድረጉ በተጨማሪ የትራፊክ አደጋም እንዲቀንስ ስለሚያግዝ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ሲሉ ተናግረዋል።
ባለፉት ዓመታት በማህበራትና በአሽከርካሪዎች ይሁንታ ላይ ተመስርቶ የቆየው የትራንስፖርት አገልግሎት ተሳፋሪዎችን ለችግር ዳርጓቸው መቆየቱን የተናገሩት ደግሞ የወላይታ ሶዶ ከተማ መናኸሪያ ኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት ስራ አስኪያጅ አቶ ኢያሱ ካፒቴን ናቸው።

ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ ታስቦ ወደ ኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት ከተገባ ሁለት ወራት ማለፉን ጠቁመው ይህ አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህ ተሳፋሪዎች ያነሱት የነበረው ከታሪፍ በላይ ክፍያና መጉላላት ቀንሶ ለህዝቡ እፎይታ መስጠቱን ተናግረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ ምክትልና የትራንስፖርት ዘርፍ ኃላፊ ብርሃኑ ጌቦ (ዶ/ር) እንደገለጹት በወላይታ ሶዶ እና ሳውላ ከተሞች መናኸሪያዎች የተጀመረው የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት የትራፊክ ፍሰቱን በማሳለጥ ከእንግልት የፀዳ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል።

በሁለቱ መናኸሪያዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ የተሻለ ለውጥ መመልከት ችለናል ያሉት ኃላፊው አገልግሎቱ ህገወጥ የታሪፍ ክፍያን እና የተሳፋሪዎችን ጊዜ በመቆጠብ የትራፊክ ፍሰቱን ማሳለጡን ተናግረዋል።
በመሆኑም በክልሉ 12 ዞኖች ዋና ዋና ከተሞች አገልግሎቱን ለማስጀመር ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን አንስተዋል።
ሁሉም ተሳፋሪዎች ኢ-ቲኬት ይዘው እንዲወጡ መደረጉ የግል ጥቅማቸውን ያስቀረባቸው የተሽከርካሪ ማህበራት የሚፈጥሩትን ችግር ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።
በመሆኑም የትራንስፖርት አገልግሎት ችግሮችን ለመቅረፍና የተገልጋዩን ማህበረሰብ እርካታ ቀጣይነት ለማረጋገጥ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንደሚያስፈልግም ኃላፊው ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025