የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በመናኸሪያው በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር መዘርጋቱ ከእንግልትና ከታሪፍ በላይ ከመክፈል ታድጎናል-ተገልጋዮች

Nov 7, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ስዶ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ መናኸሪያ የተጀመረው በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር ከእንግልት እና አግባብ ካልሆነ የታሪፍ ክፍያ ታድጎናል ሲሉ የመናኸሪያው ተገልጋዮች ተናገሩ።

በወላይታ ሶዶ ከተማ የተጀመረው የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት ዙሪያ ኢዜአ ተገልጋዮችን አነጋግሯል።

ተገልጋዮቹ እንዳሉት፤ በከተማዋ መናኸሪያ የተጀመረው በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር ከዚህ ቀደም ይገጥማቸው የነበረን ከታሪፍ በላይ የመክፈልና አላስፈላጊ እንግልት አስቀርቶላቸዋል።

አቶ ብሩክ ዘውዴ ከዚህ ቀደም የትራንስፖርት አገልግሎቱ ካለመዘመኑ የተነሳ ለተለያዩ ችግሮች ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል።

በቴክኖሎጂ የተደገፈ የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህ ያለአግባብ ይደርስብን የነበረው እንግልትና የታሪፍ በላይ ክፍያ ከማስቀረት ባሻገር ጊዜያችንን ቆጥቦልናል ብለዋል።

ሌላኛዋ ተገልጋይ ወይዘሮ የእናትፋንታ ኢያሱ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም ትክክለኛውን ታሪፍ እንኳን ለማወቅ ይቸገሩ እንደነበር አስታውሰው የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት በርካታ መረጃዎችን መዝግቦ በመያዙ ሳይጨናነቁ እና ትርፍ ሳይከፍሉ መገልገል መጀመራቸውን ገልጸዋል።

ተሽከርካሪዎችም ትርፍ መጫን ስለማይችሉ እና ወጪ ወራጅ ስለማይበዛ ወዳሰብንበት ቦታ በጊዜ እንድንደርስ ከማድረጉ በተጨማሪ የትራፊክ አደጋም እንዲቀንስ ስለሚያግዝ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ሲሉ ተናግረዋል።

ባለፉት ዓመታት በማህበራትና በአሽከርካሪዎች ይሁንታ ላይ ተመስርቶ የቆየው የትራንስፖርት አገልግሎት ተሳፋሪዎችን ለችግር ዳርጓቸው መቆየቱን የተናገሩት ደግሞ የወላይታ ሶዶ ከተማ መናኸሪያ ኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት ስራ አስኪያጅ አቶ ኢያሱ ካፒቴን ናቸው።


ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ ታስቦ ወደ ኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት ከተገባ ሁለት ወራት ማለፉን ጠቁመው ይህ አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህ ተሳፋሪዎች ያነሱት የነበረው ከታሪፍ በላይ ክፍያና መጉላላት ቀንሶ ለህዝቡ እፎይታ መስጠቱን ተናግረዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ ምክትልና የትራንስፖርት ዘርፍ ኃላፊ ብርሃኑ ጌቦ (ዶ/ር) እንደገለጹት በወላይታ ሶዶ እና ሳውላ ከተሞች መናኸሪያዎች የተጀመረው የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት የትራፊክ ፍሰቱን በማሳለጥ ከእንግልት የፀዳ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል።


በሁለቱ መናኸሪያዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ የተሻለ ለውጥ መመልከት ችለናል ያሉት ኃላፊው አገልግሎቱ ህገወጥ የታሪፍ ክፍያን እና የተሳፋሪዎችን ጊዜ በመቆጠብ የትራፊክ ፍሰቱን ማሳለጡን ተናግረዋል።

በመሆኑም በክልሉ 12 ዞኖች ዋና ዋና ከተሞች አገልግሎቱን ለማስጀመር ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን አንስተዋል።

ሁሉም ተሳፋሪዎች ኢ-ቲኬት ይዘው እንዲወጡ መደረጉ የግል ጥቅማቸውን ያስቀረባቸው የተሽከርካሪ ማህበራት የሚፈጥሩትን ችግር ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

በመሆኑም የትራንስፖርት አገልግሎት ችግሮችን ለመቅረፍና የተገልጋዩን ማህበረሰብ እርካታ ቀጣይነት ለማረጋገጥ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንደሚያስፈልግም ኃላፊው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026