የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የክልሎችን መልከዓ ምድራዊና ተፈጥሯዊ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ የሆርቲካልቸር ፓርኮች ይገነባሉ

Nov 7, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፡-የክልሎችን መልከዓ ምድራዊና ተፈጥሯዊ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ የሆርቲካልቸር ፓርኮች እንደሚገነቡ በግብርና ሚኒስቴር የሆርቲካልቸር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አብደላ ነጋሽ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ሸዋ አካባቢ ያለውን የግብርና ሁኔታ በተመለከቱበት ወቅት የሆርቲካልቸር ዘርፉን ለማሳደግ የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አስታውቀዋል።

አርሶ አደሮች የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብዓት አቅርቦትንና የተሻሻሉ ዝርያዎችን በስፋት መጠቀም መቻላቸው በአንድ ሄክታር የሚገኘው ምርት እንዲጨምር አስችሏል ብለዋል፡፡

እንዲሁም በክላስተር የሚከናወነው የግብርና ስራ የሚገኘውን ምርት ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል።

በተለይም የፓፓያ፣ የአቦካዶና የሙዝ ምርቶችን በምርምር በማሳደግ የተሻለ ገቢ ማግኘት እንደሚቻል መመልከታቸውን ነው የገለጹት።

ይህም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት በእጅጉ እንደሚያግዝ በመስክ ጉብኝቱ ላይ ገልጸዋል።

በግብርና ሚኒስቴር የሆርቲካልቸር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አብደላ ነጋሽ እንደገለጹት፤ የሆርቲካልቸር ዘርፉን በሚፈለገው ልክ ለማልማት እየተሰራ ነው።

በዚህም አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርግና ዘርፉን በተሻለ መልኩ የሚለውጥ ሀገራዊ ስትራቴጂ ስራ ላይ መዋሉንም አስታውቀዋል።

ስትራቴጂው በሆርቲካልቸር ዘርፍ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።

ስትራቴጂው የሆርቲካልቸር ፓርኮችን መመስረት ታሳቢ ማድረጉን ጠቅሰው፥ይህም በተለይ አነስተኛ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል።

ስትራቴጂው በዘርፉ ያለውን ማነቆ በመፍታት በመስኩ የሚፈሰውን መዋዕለ ንዋይ ለማሳደግ እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡

በአገር ደረጃ በተያዘው ግብ የክልሎችን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ 10 ቦታዎች ላይ የሆርቲካልቸር ፓርኮች እንደሚገነቡ ነው የተናገሩት።

ግንባታ የተጀመረባቸው ክልሎች መኖራቸውንም ነው የጠቆሙት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026