🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፡-የክልሎችን መልከዓ ምድራዊና ተፈጥሯዊ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ የሆርቲካልቸር ፓርኮች እንደሚገነቡ በግብርና ሚኒስቴር የሆርቲካልቸር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አብደላ ነጋሽ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ሸዋ አካባቢ ያለውን የግብርና ሁኔታ በተመለከቱበት ወቅት የሆርቲካልቸር ዘርፉን ለማሳደግ የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አስታውቀዋል።
አርሶ አደሮች የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብዓት አቅርቦትንና የተሻሻሉ ዝርያዎችን በስፋት መጠቀም መቻላቸው በአንድ ሄክታር የሚገኘው ምርት እንዲጨምር አስችሏል ብለዋል፡፡
እንዲሁም በክላስተር የሚከናወነው የግብርና ስራ የሚገኘውን ምርት ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል።
በተለይም የፓፓያ፣ የአቦካዶና የሙዝ ምርቶችን በምርምር በማሳደግ የተሻለ ገቢ ማግኘት እንደሚቻል መመልከታቸውን ነው የገለጹት።
ይህም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት በእጅጉ እንደሚያግዝ በመስክ ጉብኝቱ ላይ ገልጸዋል።
በግብርና ሚኒስቴር የሆርቲካልቸር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አብደላ ነጋሽ እንደገለጹት፤ የሆርቲካልቸር ዘርፉን በሚፈለገው ልክ ለማልማት እየተሰራ ነው።
በዚህም አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርግና ዘርፉን በተሻለ መልኩ የሚለውጥ ሀገራዊ ስትራቴጂ ስራ ላይ መዋሉንም አስታውቀዋል።
ስትራቴጂው በሆርቲካልቸር ዘርፍ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።
ስትራቴጂው የሆርቲካልቸር ፓርኮችን መመስረት ታሳቢ ማድረጉን ጠቅሰው፥ይህም በተለይ አነስተኛ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል።
ስትራቴጂው በዘርፉ ያለውን ማነቆ በመፍታት በመስኩ የሚፈሰውን መዋዕለ ንዋይ ለማሳደግ እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡
በአገር ደረጃ በተያዘው ግብ የክልሎችን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ 10 ቦታዎች ላይ የሆርቲካልቸር ፓርኮች እንደሚገነቡ ነው የተናገሩት።
ግንባታ የተጀመረባቸው ክልሎች መኖራቸውንም ነው የጠቆሙት።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026