🔇Unmute
አሶሳ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በማልማት የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር አመራሮች በተገኙበት የክልሉን ፀጋዎች አልምቶ መጠቀም በሚቻልበት መንገድ ላይ የውይይት መድረክ አካሂደዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ ላይ ባቀረቡት የመወያያ ሰነድ በክልሉ የአካባቢውን ፀጋዎችን በማልማት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በክልሉ ገቢዎችን አሟጦ በመሰብሰብ የራስን ወጪ በራስ አቅም በመሸፈን ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶችን ማከናወን ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በማልማት የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር የክልሉን ኢኮኖሚ ማሳደግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ከለውጡ ወዲህ በግብርና፣ በማዕድንና ሌሎች ዘርፎች በክልሉ የተገኙ ውጤቶችን በተቀናጀ መልኩ ማስቀጠል ይገባል ያሉት አቶ አሻድሊ፤ በዚህ ረገድ አመራሩ በላቀ ቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በክልሉ የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ማስፋት፤ ጠንካራ ተቋማት ግንባታ እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከልን አጠናክሮ በመቀጠል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባም አሳስበዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025