🔇Unmute
አሶሳ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በማልማት የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር አመራሮች በተገኙበት የክልሉን ፀጋዎች አልምቶ መጠቀም በሚቻልበት መንገድ ላይ የውይይት መድረክ አካሂደዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ ላይ ባቀረቡት የመወያያ ሰነድ በክልሉ የአካባቢውን ፀጋዎችን በማልማት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በክልሉ ገቢዎችን አሟጦ በመሰብሰብ የራስን ወጪ በራስ አቅም በመሸፈን ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶችን ማከናወን ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በማልማት የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር የክልሉን ኢኮኖሚ ማሳደግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ከለውጡ ወዲህ በግብርና፣ በማዕድንና ሌሎች ዘርፎች በክልሉ የተገኙ ውጤቶችን በተቀናጀ መልኩ ማስቀጠል ይገባል ያሉት አቶ አሻድሊ፤ በዚህ ረገድ አመራሩ በላቀ ቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በክልሉ የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ማስፋት፤ ጠንካራ ተቋማት ግንባታ እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከልን አጠናክሮ በመቀጠል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባም አሳስበዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026