የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኮርፖሬሽኑ በ20 ሺህ ሔክታር ላይ የደረሱ የምርጥ ዘር ሰብሎችን እየሰበሰበ ነው

Nov 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 3/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ20 ሺህ ሔክታር ላይ የደረሱ የምርጥ ዘር ሰብሎችን እየሰበሰበ መሆኑን አስታወቀ።

የኮርፖሬሽኑ የኮሙኒኬሽንና ማኅበራዊ ኃላፊነት ሥራ አመራር ሥራ አስኪያጅ ጋሻው አይችሉህም ለኢዜአ እንዳሉት፥ ተቋሙ በራሱ የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻዎች እንዲሁም በኮንትራት ዘር አባዥ እርሻ (በሰፋፊ የባለሃብቶች እርሻ)፣ በክላስተር በተደራጁ አርሶ አደሮች ማሳ እና በሦስት የግብርና ቴክኒክና ሞያ ትምህርት ሥልጠና ኮሌጆች እርሻ የተባዙ ሰብሎችን እየሰበሰበ ነው።

በአጠቃላይ በ20 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የተባዙ የ22 ሰብሎች 90 ዝርያዎች ምርት እየተሰበሰበ ይገኛል ብለዋል።

ኮርፖሬሽኑ በ2017/18 የምርት ዘመን ለማባዛት ያቀደው 460 ሺህ ኩንታል ዘር መሆኑንም አስታውቀዋል።

በሀገር ደረጃ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማሳካት እየተደረገ በሚገኘው ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴ ውስጥ ኮርፖሬሽኑ የግብርና ግብዓቶችንና ዘመናዊ የእርሻ መሣሪያዎችን በማቅረብ እንዲሁም የተቀናጀ የሜካናይዜሽን አገልግሎት በመስጠት ግምባር ቀደም ሚና እየተጫወተ ይገኛል ሲሉም ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026