የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የልማት ፕሮጀክቶቹ የኢትዮጵያን መጻኢ ዕድል የተሻለ ለማድረግ ጉልህ ሚና አላቸው

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-በመንግሥት ይፋ የተደረጉት ግዙፍ ሀገራዊ ልማት ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን መጻኢ ዕድል የተሻለ በማድረግ ሁሉን አቀፍ እድገት የሚያረጋግጡ ናቸው ሲሉ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባ ያበሰሯቸው የ30 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ከመሰረተ ልማት ግንባታ በላይ የኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያረጋግጡ መሆናቸው ነው የተመላከተው።

የጉባ ብስራት ከሆኑ ፕሮጀክቶች መካከል የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ፣ የኒውክሌር ማበልጸጊያ፣ ግዙፉ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ፣የጋዝ ፋብሪካ፣የነዳጅ ማጣሪያ እንዲሁም ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን በላይ ቤቶች ግንባታ ይገኙበታል።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረጉ የልማት ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን መጻኢ ዕድል የተሻለ ለማድረግ ጉልህ ሚና አላቸው ብለዋል።

የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አበራ በቀለ፣ኢትዮጵያውያን ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በራሳቸው አቅም ማሳካት እንደሚችሉ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።


በመንግሥት የተያዙት ትላልቅ ፕሮጀክቶችም የኢትዮጵያን የማድረግ አቅም የሚያሳድጉ በመሆናቸው እንደ ፓርቲ እንደግፋቸዋለን ብለዋል።

የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የውጭና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ መብራቱ ዓለሙ (ዶ/ር)፤ መንግሥት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመራቸው ፕሮጀክቶች ሁሉን አቀፍ ዕድገት የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል።


የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ቀጄላ መርዳሳ በበኩላቸው፤ እንደሀገር እየተተገበሩ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ገልጸው፤ ለተግባራዊነቱ ድጋፍ እንደሚያደርጉም ተናግረዋል።


የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አበራ በቀለ፣የፕሮጀክቶቹ እውን መሆን የኢትዮጵያን መጻኢ ዕድል የተሻለ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የውጭና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ መብራቱ ዓለሙ (ዶ/ር) ፓርቲዎች መንግስት የሚያከናውናቸው የልማት ሥራዎች ላይ የድርሻቸውን እንዲወጡ ህጋዊ የአሰራር ማዕቀፍ መዘርጋት ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026