🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ለከተሞች ብልጽግና እና ማንሰራራት መልካም አሻራ መጣሉን የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ ገለጹ።
10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም "የከተሞች ዕድገት ለኢትዮጵያ ልህቀት" በሚል መሪ ቃል በአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ሲካሄድ ቆይቷል።በዛሬው እለትም የፎረሙ የማጠቃለያ መርሀግብር ተካሂዷል።

በመድረኩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ፣የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ታድመዋል።
የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ በዚሁ ወቅት ፤ 10ኛው የከተሞች ፎረም የመደመር እሳቤ በተግባር የታየበት መሆኑን ተናግረዋል።
የፎረሙ ታዳሚዎች በአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ስኬታማ ቆይታ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

ፎረሙ ከተሞች ልምዳቸውን የተካፈሉበት አንዱ ከሌላው ትምህርት የወሰደበት መሆኑንም ተናግረዋል።
ለከተሞች ብልጽግና እና ማንሰራራት መልካም አሻራ መጣሉን ገልጸው፤ ፎረሙ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026