🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ለከተሞች ብልጽግና እና ማንሰራራት መልካም አሻራ መጣሉን የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ ገለጹ።
10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም "የከተሞች ዕድገት ለኢትዮጵያ ልህቀት" በሚል መሪ ቃል በአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ሲካሄድ ቆይቷል።በዛሬው እለትም የፎረሙ የማጠቃለያ መርሀግብር ተካሂዷል።

በመድረኩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ፣የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ታድመዋል።
የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ በዚሁ ወቅት ፤ 10ኛው የከተሞች ፎረም የመደመር እሳቤ በተግባር የታየበት መሆኑን ተናግረዋል።
የፎረሙ ታዳሚዎች በአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ስኬታማ ቆይታ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

ፎረሙ ከተሞች ልምዳቸውን የተካፈሉበት አንዱ ከሌላው ትምህርት የወሰደበት መሆኑንም ተናግረዋል።
ለከተሞች ብልጽግና እና ማንሰራራት መልካም አሻራ መጣሉን ገልጸው፤ ፎረሙ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025