🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ለከተሞች ብልጽግና እና ማንሰራራት መልካም አሻራ መጣሉን የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ ገለጹ።
10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም "የከተሞች ዕድገት ለኢትዮጵያ ልህቀት" በሚል መሪ ቃል በአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ሲካሄድ ቆይቷል።በዛሬው እለትም የፎረሙ የማጠቃለያ መርሀግብር ተካሂዷል።

በመድረኩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ፣የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ታድመዋል።
የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ በዚሁ ወቅት ፤ 10ኛው የከተሞች ፎረም የመደመር እሳቤ በተግባር የታየበት መሆኑን ተናግረዋል።
የፎረሙ ታዳሚዎች በአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ስኬታማ ቆይታ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

ፎረሙ ከተሞች ልምዳቸውን የተካፈሉበት አንዱ ከሌላው ትምህርት የወሰደበት መሆኑንም ተናግረዋል።
ለከተሞች ብልጽግና እና ማንሰራራት መልካም አሻራ መጣሉን ገልጸው፤ ፎረሙ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026