የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ማህበራት በሌማት ትሩፋት መርሐግብር ተጠቃሚ ሆነዋል

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ይርጋ ጨፌ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-በሌማት ትሩፋት መርሀግብር የቤተሰብ የምግብ ፍጆታን ከመሸፈን ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን በጌዴኦ ዞን ይርጋ ጨፌ ከተማ በልማቱ የተሰማሩ ማህበራት ገለጹ።

በከተማው መርሀግብሩን ከሥራ ዕድል ፈጠራ ጋር በማስተሳሰር ከ6 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑም ተመላክቷል።


ከሦስት ዓመት በፊት በአርባ ምንጭ ከተማ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረገው የሌማት ትሩፋት መርሀግብር በምግብ ሉአላዊነትን ማስከበርና ክብርን ከማረጋገጥ ጋር የተያያዘ ነው።

ዓላማውም በሥጋ፣ በእንቁላል፣ በማርና ወተት የተትረፈረፈ ምርት በማምረት መጠቀምና የገቢ ምንጭ ማድረግ ነው።


መርሀግብሩ ይፋ መደረጉን ተከትሎ ባለፉት ሦስት ዓመታት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በልማቱ የተሳተፉ በርካቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መጥተዋል።

በጌዴኦ ዞን ይርጋ ጨፌ ከተማም በመርሀግብሩ የተሳተፉ ማህበራት ከዘመናዊ እንስሳት እርባታ እና ንብ ማነብ ሥራቸው ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ነው የገለጹት።

በመርሀግብሩ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ አቅርቦትን ከማረጋገጥ ባለፈ ለአካባቢ ገበያ በማቅረብ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡት መካከል አቶ አበባው አዳነ፤ በተሻሻሉ የወተት ላሞች እርባታ እና በንብ ማነብ ዘርፍ መሰማራታቸውን ገልጸዋል።


ከአርባ በሚበልጡ ዘመናዊና ባህላዊ የንብ ቀፎዎች የሚያመርቱትን ማር ከቤት ውስጥ ፍጆታ አልፈው ለገበያ በዓመት ከ35 ኪሎ ግራም በላይ የተጣራ ማር እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ ጎን ለጎን ከዘጠኝ የተሻሻሉ ላሞች በቀን ከአንድ ላም ብቻ በአማካይ እስከ 15 ሊትር ወተት እንደሚያገኙ ተናግረዋል።

ከልማት ሥራው ተጠቃሚ ከመሆናቸው በተጨማሪ ለአምስት ሰዎች የሥራ እድል መፍጠራቸውን ገልጸዋል።

ባለፈው ዓመት ከመንግስት ባገኙት የ150 ሺህ ብር ብድር አምስት ሆነው በአንድ ቀን የዶሮ ጫጩት እርባታ ሥራ እንደተሰማሩና ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን የገለጸው ደግሞ የብቁ ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ድጋፌ ተፈሪ ነው።


ከአስር ሺህ በላይ የአንድ ቀን ጫጩቶችን በመረከብ 45 ቀን ሲሞላቸው ለሽያጭ በማቅረብ ትርፋማ መሆናቸውን ተናግሯል።

በአሁኑ ወቅት የተበደሩትን ገንዘብ ከመመለስ ባለፈ ከ125 ሺህ ብር በላይ በባንክ ተቀማጭ ማድርጋቸውን ተናግሯል።

የሌማት ትሩፋት መርሀግብር በአካባቢያቸው ያለውን ጸጋ ተጠቅመው እንዲለወጡ እድል መፍጠሩን የተናገረው ደግሞ የድል በትግል የንብ አናቢ ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ኤርሚያስ ጥላሁን ነው።


በተለይ በይርጋጨፌና አካባቢው በጥምር ግብርና ቡና የሚመረት መሆኑ ለንብ ማነብ ሥራ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንና በዘርፉ ተሰማርተው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግሯል።

ከዘመናዊ የንብ ቀፎዎች ከ500 ኪሎ ግራም በላይ ድፍድፍና የተጣራ ማር ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሶ በቀጣይ በንግስት ንብ ብዜት ሥራ የመሰማራት ዕቅድ እንዳላቸው ጠቁሟል።

የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የሥራና ክህሎት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ዮሴፍ አየለ በበኩላቸው፤ በከተማው በሌማት ትሩፋት በተለይም በማር፣ በወተትና በዶሮ እርባታ ከ20 በላይ ማህበራት ወደ ሥራ መግባታቸውን ገልጸዋል።


ለማህበራቱ በተመቻቹ ሼዶች ምርቶቻቸውን ለገበያ እያቀረቡ መሆኑን ገልጸው፣ የሌማት ትሩፋት ስርዓተ ምግብን ከማሻሻል በተጨማሪ የእንስሳት ተዋፅኦ ምርታማነትን እያሳደገው መምጣቱን ጠቅሰዋል፡፡

በተያዘው ዓመት ብቻ ከ2 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ የተጣራ ማር ለገበያ መቅረቡን የተናገሩት አቶ ዮሴፍ፣ መርሀግብሩ ገበያን ለማረጋጋት እያገዘ መሆኑንም ተናግረዋል።

ልማቱን ለማጠናከር ዘንድሮ ከ6 ሺህ በላይ ወጣቶችን በዘርፉ ለማሰማራት የወጣቶች ልየታ፣ የመስሪያ ቦታና የብድር አቅርቦት መመቻቸቱንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025