🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ የማሌዢያ ኩባንያዎች የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎች የሚጠቀሙበት ምቹ ምኅዳር መኖሩን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ።
የኢትዮጵያ ማሌዢያ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ ተካሂዷል።

በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል በተካሄደው ፎረም ላይ የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሴሪ አንዋር ኢብራሂም፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና የንግድና ኢንቨስትመንት አልሚ ባለሃብቶች ተገኝተዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጉብኝት በሀገራቱ መካከል ያለውን የንግድ ትስስር በማጠናከር የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱን ለማጎልበት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
ኢትዮጵያና ማሌዢያ ያሏቸው ብዝኅ ሕብረ ብሔራዊነትን የተላበሱ የጋራ እሴቶች ለጋራ ዕድገትና ቀጣናዊ ትብብር ልዩ ዕድል መሆናቸውንም ገልጸዋል።
እ.አ.አ በ1965 የተጀመረውን የሀገራቱን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ፕሬዝዳንት ታዬ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በማድረግ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የኢንቨስትመንት ሥነ-ምኅዳር መገንባቷን አስረድተዋል።
በግብርና መስክም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትክክለኛው የልማት መንገድ ላይ እየተጓዘች እንደምትገኝ ፕሬዝዳንት ታዬ አብራርተዋል።

በዚህም ሁለቱ ሀገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በማዕድንና በሌሎች ወሳኝ የልማት መስኮች ያላቸውን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።
የማሌዢያ ኩባንያዎች የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎች በመጠቀም የጋራ ብልጽግና እና ተጠቃሚነትን የሚወስን የልማት ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
ማሌዢያ ከዲፕሎማሲ ባለፈ የንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነቷን ለማስፋት እያከናወነች ያለው ስራ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል።
የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሴሪ አንዋር ኢብራሂም የሀገራቱን ሁለንተናዊ ትብብር ለማጠናከር ላሳዩት ቁርጠኝነት ምስጋና አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026