የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጉዳያችንን በአጭር ግዜ መጨረስ አስችሎናል - ተገልጋዮች

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ህዳር 14/2018(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ መጨረስ እንዳስቻላቸው በሀዋሳ ከተማ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች ገለጹ።

በሲዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የ12 ተቋማት 38 አገልግሎቶች እየተሰጠ መሆኑን የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር አስታውቀዋል።

የሲዳማ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ ከጀመረበት መስከረም አጋማሽ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ለ1ሺህ 300 ሰዎች አገልግሎት መስጠቱ ተገልጿል።

በማዕከሉ የሲዳማ ክልል ንግድ ቢሮ፣ ገቢዎች ባለስልጣን፣ ጤና ቢሮ እና የሀዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን ጨምሮ የ12 ተቋማት አገልግሎቶች በማዕከሉ ይሰጣሉ።

እነዚህ ተቋማት በአንድ ማዕከል ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠታቸው እንግልት፣ አላስፈላጊ ወጪና ጊዜ በመቆጠብ ተጠቃሚ እንዳደረጋቸውም ተገልጋዮች ገልጸዋል።

ኢዜአ በማዕከሉ ጉዳያቸውን ሲያስፈጽሙ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች እንደገለጹት ቀደም ሲል በተበታተነ ስፍራ ሲሰጡ የነበሩ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል ውስጥ ማግኘታቸው ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ መጨረስ አስችሏቸዋል።


በማዕከሉ አገልግሎት ለማግኘት የመጡት ወይዘሮ የሺመቤት ተረፈ እንዳሉት ቀደም ሲል በተለያዩ ቦታዎች ሲሰጡ የነበሩ የመንግስት አገልግሎቶችን በአንድ ስፍራ እያገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የማዕከሉ አገልግሎት ረጅም ውረፋ ከማስቀረት ባለፈ የተገልጋይን እንግልትና የሚባክን ጊዜ ማስቀረቱን ገልጸዋል።


ውክልና ለመስጠት ወደ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ እንደመጡ የገለጹት ሌላው አስተያየት ሰጪ ሄኖክ አደራ በበኩላቸው በማዕከሉ ፈጣን አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

ከበር ጀምሮ ጥሩ መስተንግዶ ማግኘታቸውን ጠቁመው፣ ማዕከሉ ከቀበሌ ጀምሮ ወደ ተለያዩ ተቋማት ሲመላለሱ ሲገጥማቸው የነበረን እንግልት የበዛበት አሰራርን ማስቀረቱንና ባገኙት አገልግሎት መደሰታቸውን ገልጸዋል።


በማዕከሉ አገልግሎት እየሰጡ ካሉ ተቋማት የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን ባለሙያ እንዳሻው ኤራንጎ ቀደም ሲል ደንበኞች ቲን ቁጥር ለማግኘት ወደ ባለስልጣኑ ሲመጡ አሻራ ሰጥተው የፋይዳ መታወቂያ እንዲያወጡ ኢትዮ ቴሌኮም እንልካቸው ነበር ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት ግን በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተለያዩ አገልግሎቶች ስለሚሰጡ ተገልጋዩ ሁሉንም አገልግሎቶች በማዕከሉ እያገኘ በመሆኑ ተጠቃሚ መሆኑን ገልጸዋል።


የሲዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እንግዳየሁ ዘውዴ እንዳሉት በማዕከሉ 12 የፌዴራል፣ የሲዳማ ክልልና የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ተቋማት 38 አገልግሎቶችን ይሰጣሉ።

ማዕከሉ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ወዲህ እስካሁን ድረስ ለ1ሺህ 300 ተገልጋዮች አገልግሎት መስጠቱን ጠቅሰው፣ ተገልጋዩ ባገኘው አገልግሎት ላይ በሰጠው አስተያየትና እርካታ እያገኘ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026