🔇Unmute
ከሚሴ፤ ሕዳር 16/2018(ኢዜአ)፦ በተያዘው ዓመት በበጋ መስኖ ስንዴ ከ4 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት እንደሚለማ ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትሩ አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል፣ የአማራ ክልል እና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋ ጨፋ ወረዳ የበጋ መስኖ ስንዴ የዘር ስራን ዛሬ አስጀምረዋል።

የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በማስጀመሪያው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለፁት፣ እንደ ሀገር በዘንድሮው ዓመት ከ4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት የዘር ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
በሜካናይዜሽን በታገዝ መንገድ ከሚለማው የመስኖ ልማት ከ175 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት እንደሚጠበቅም ገልጸዋል።
አስካሁን በተደረገ እንቅስቃሴም ከ1 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈን መቻሉን አስረድተዋል።

የስንዴ ልማቱን ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥና ለውጭ ገበያ የማቅረብ ተግባር በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል።
ለዚህም ከዚህ ቀደም በስንዴ ለምቶ የማያውቅ መሬትን ወደ ልማት ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
ዛሬ በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን እየተካሄደ ያለው የበጋ መስኖ ስንዴ ዘር ስራም የዚሁ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ በክልሉ ከ350 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት እየተሰራ ነው።

ከመስኖ ልማቱ ከ13 ነጥብ 6 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱን ጠቁመው፤ ምርታማነትን ለማሳደግ የግብዓትና የቴክኖሎጂ አቅርቦት እየተደረገ ነው ብለዋል።
የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በወቅቱ እንደገለፁት፣ የመስኖ ልማቱን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ በምግብ ራስን ከመቻል አልፎ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት እየተሰራ ነው።

በዚህም በተያዘው የበጋ ወራት ከ12 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ሰብል ለማልማት ታቅዶ የዘር ስራ መጀመሩን ገልጸዋል።
ለአርሶ አደር ቴክኖሎጂ እና ግብዓት በማቅረብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ምርቱን ለገበያ እንዲያቀርብ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025