የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በሀገር አቀፍ ደረጃ በበጋ መስኖ ስንዴ ከ4 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት ይለማል

Nov 26, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ከሚሴ፤ ሕዳር 16/2018(ኢዜአ)፦ በተያዘው ዓመት በበጋ መስኖ ስንዴ ከ4 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት እንደሚለማ ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትሩ አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል፣ የአማራ ክልል እና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋ ጨፋ ወረዳ የበጋ መስኖ ስንዴ የዘር ስራን ዛሬ አስጀምረዋል።


የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በማስጀመሪያው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለፁት፣ እንደ ሀገር በዘንድሮው ዓመት ከ4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት የዘር ስራ እየተከናወነ ይገኛል።

በሜካናይዜሽን በታገዝ መንገድ ከሚለማው የመስኖ ልማት ከ175 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት እንደሚጠበቅም ገልጸዋል።

አስካሁን በተደረገ እንቅስቃሴም ከ1 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈን መቻሉን አስረድተዋል።


የስንዴ ልማቱን ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥና ለውጭ ገበያ የማቅረብ ተግባር በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል።

ለዚህም ከዚህ ቀደም በስንዴ ለምቶ የማያውቅ መሬትን ወደ ልማት ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

ዛሬ በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን እየተካሄደ ያለው የበጋ መስኖ ስንዴ ዘር ስራም የዚሁ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ በክልሉ ከ350 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት እየተሰራ ነው።


ከመስኖ ልማቱ ከ13 ነጥብ 6 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱን ጠቁመው፤ ምርታማነትን ለማሳደግ የግብዓትና የቴክኖሎጂ አቅርቦት እየተደረገ ነው ብለዋል።

የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በወቅቱ እንደገለፁት፣ የመስኖ ልማቱን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ በምግብ ራስን ከመቻል አልፎ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት እየተሰራ ነው።


በዚህም በተያዘው የበጋ ወራት ከ12 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ሰብል ለማልማት ታቅዶ የዘር ስራ መጀመሩን ገልጸዋል።

ለአርሶ አደር ቴክኖሎጂ እና ግብዓት በማቅረብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ምርቱን ለገበያ እንዲያቀርብ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026