🔇Unmute
ከሚሴ፤ ሕዳር 16/2018(ኢዜአ)፦ በተያዘው ዓመት በበጋ መስኖ ስንዴ ከ4 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት እንደሚለማ ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትሩ አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል፣ የአማራ ክልል እና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋ ጨፋ ወረዳ የበጋ መስኖ ስንዴ የዘር ስራን ዛሬ አስጀምረዋል።

የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በማስጀመሪያው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለፁት፣ እንደ ሀገር በዘንድሮው ዓመት ከ4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት የዘር ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
በሜካናይዜሽን በታገዝ መንገድ ከሚለማው የመስኖ ልማት ከ175 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት እንደሚጠበቅም ገልጸዋል።
አስካሁን በተደረገ እንቅስቃሴም ከ1 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈን መቻሉን አስረድተዋል።

የስንዴ ልማቱን ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥና ለውጭ ገበያ የማቅረብ ተግባር በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል።
ለዚህም ከዚህ ቀደም በስንዴ ለምቶ የማያውቅ መሬትን ወደ ልማት ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
ዛሬ በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን እየተካሄደ ያለው የበጋ መስኖ ስንዴ ዘር ስራም የዚሁ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ በክልሉ ከ350 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት እየተሰራ ነው።

ከመስኖ ልማቱ ከ13 ነጥብ 6 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱን ጠቁመው፤ ምርታማነትን ለማሳደግ የግብዓትና የቴክኖሎጂ አቅርቦት እየተደረገ ነው ብለዋል።
የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በወቅቱ እንደገለፁት፣ የመስኖ ልማቱን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ በምግብ ራስን ከመቻል አልፎ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት እየተሰራ ነው።

በዚህም በተያዘው የበጋ ወራት ከ12 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ሰብል ለማልማት ታቅዶ የዘር ስራ መጀመሩን ገልጸዋል።
ለአርሶ አደር ቴክኖሎጂ እና ግብዓት በማቅረብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ምርቱን ለገበያ እንዲያቀርብ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026