🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 17/2018(ኢዜአ)፦ ምርታማነታቸው ከፍ ያሉና በሽታን መከላከል የሚችሉ የተለያዩ ምርጥ የሰብል ዝርያዎችን በማባዛት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ እያደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአሰላ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ገለጸ።
ኮርፖሬሽኑ ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነት በእጥፍ ለማሳደግ ከምንጊዜውም በላይ በትኩረት እየሠራ መሆኑንም አስታውቋል።
ኮርፖሬሽኑ በ2017/18 የምርት ዘመን በአጠቃላይ በ20ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የተባዙ የ22 ሰብሎች 90 ዝርያዎች ምርት እየሰበሰበ ሲሆን፣ ለማባዛት ያቀደው 460ሺህ ኩንታል ዘር መሆኑም ተጠቁሟል።
በኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአሰላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ ተወካይ ማንያዘዋል ለማ እንዳሉትም ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ አርሶ አደሩ ከመሬት ዝግጅት እስከ ጎተራ በሚያደርገው የእርሻ እንቅስቃሴ ውስጥ ግብዓቶችን በማቅረብ ነው።

ጽሕፈት ቤቱ የስንዴ፣ የጤፍ እና የሌሎችም ሰብሎች ምርጥ ዝርያዎችን እያባዛ በመላው የሀገሪቱ አካባቢዎች ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ በ2017/18 በቅድመ መስራች፣ መስራች እና የተመሰከረለት የተባሉ ምርጥ ዘሮችን በ1ሺህ 964 ሄክታር መሬት ላይ እያባዛ መሆኑን ተናግረዋል።
ከዚህም 49ሺህ 205 ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱን አስታውቀዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ኮርፖሬሽኑ የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።
በቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የሚባዛው ምርጥ ዘር ከሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የአየር ንብረት ጋር የሚስማማ መሆኑን ጠቁመው፣ የሚያሰራጫቸው ምርጥ ዘሮች ከፍተኛ ምርት በማስገኘት የምርት መጠንና ጥራት የሚያሳድጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የዘር ጥራት፣ ቁጥጥርና ክትትል ቡድን መሪ አዳነ ኃይሉ በበኩላቸው፤ ኮርፖሬሽኑ ጥራት ያላቸው ዘሮች እና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ በመሆናቸው የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የበኩላቸውን መወጣት ያስችላሉ ብለዋል።
በኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአሰላ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ለበጋ መስኖ እርሻ የሚውል ከአሥራ አንድ ሺህ አምስት መቶ ኩንታል በላይ የስንዴ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ እያሰራጨ መሆኑንም አስታውቋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026