🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 21/2018 (ኢዜአ)፡-የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲያውቁና በዲጂታል ዘርፍ ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ መሠረት እንደጣለላቸው ወጣቶች ገለጹ፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገው የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ወጣቶች በኦንላይን የኮዲንግ ስልጠና የሚወስዱበት ሂደት ነው፡፡
በኢትዮጵያ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ስታርትአፖች በሀገሪቱ ፈጣን ዕድገት ለማምጣት እና ገበያውን ለመለወጥ የተያዘውን ጥረት በእጅጉ እያገዙ ይገኛሉ፡፡
ይህን ተከትሎ በርካታ ስታርታፖች በቴክኖሎጂ በመታገዝ በሚሰሯቸው ስራዎች የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ የግብርና ቴክኖሎጂ እንዲሁም የሎጂስቲክስና የኢ-ኮሜርስ ዘርፎች በስፋት ተደራሽ እንዲሆኑ እያስቻሉ ነው፡፡
ኢዜአ ያነጋገራቸው ስታርታፖች ኢኒሼቲቩ የዲጂታል አቅማቸውን በማጎልበት ተጨማሪ ክህሎት እንዲጨብጡ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
የአዲስ ኤ አይ ድርጅት መስራች ወጣት ቃልኪዳን ደምሌ፤ በቴክኖሎጂው ዘርፍ በመሰማራት ውጤታማ ስራዎችን ለማበርከት የወሰደችው የኮደርስ ስልጠና በሚገባ እንደጠቀማት ተናግራለች፡፡
በሁለት የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች የሚሰራ መተግበሪያ በመፍጠር ወደ ስራ ማስገባት መቻሏን የምትናገረው ወጣቷ ለዚህ ስኬትም ስልጠናውን መውሰዷ እንደረዳት ገልጻለች፡፡
ስልጠናው በተለይም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳደሪ ለመሆን፣ ፈጠራን ለማላቅ ብሎም የሥራ ዕድሎችን ለማግኘት እንዳስቻላት ጠቅሳለች፡፡
ያሬድ እንዳለ በበኩሉ መንግስት እያደረገላቸው በሚገኘው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ከራሳቸው አልፈው ለበርካቶች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻላቸውን ተናግሯል፡፡
የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ወጣቶች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲያውቁና በዲጂታል ዘርፍ ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ መሠረት መጣሉን ጠቅሷል፡፡
ይህም ስታርታፖች በቴክኖሎጂው ዘርፍ ራሳቸውንና ሀገራቸውን የሚለውጡ የፈጠራ ስራዎችን እንዲያበረክቱ ዕድል መፍጠሩን ተናግሯል፡፡
የፌዶ ፓወር ሶሉሽን ድርጅት ባለቤት ወጣት ፌደሳ ሹማ በበኩሉ በፈጠራ ውጤቱ በመታገዝ ችግር ፈቺ ስራዎችን በመሥራት ላይ እንደሚገኝ ተናግሯል፡፡
የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ስራው ለማሳደግ የሚረዳውን ተጨማሪ ዕውቀት በማስጨበጥ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን እንዳስቻለው ገልጿል፡፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026