🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡- ባለፉት የለውጥ ዓመታት የኢንቨስትመንት ከባቢውን መቀየር ያስቻሉ በርካታ ስኬታማ ማሻሻያዎች መከናወናቸውን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ባለፉት ሰባት ዓመታት የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዐቅም ለማሳደግ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ተነድፎ ዓይነተ-ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።
ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ከሚያተኩርባቸው ዘርፎች አንዱ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ፍሰት በይበልጥ ማሳደግ መሆኑንም አስረድተዋል።
በዚህም የኢንቨስትመንት ምኅዳሩን ለማሻሻል የተለያዩ ጥረቶች መደረጋቸውን ነው ኮሚሽነሩ የገለጹት።
ከነዚህ መካከል የሕግ ማሻሻያ በማድረግ የኢንቨስትመንት ከባቢውን ተገማች እና ግልጽ ወደሆነ የኢንቨስትመንት ዐውድ ለመቀየር ያስቻሉ ከ120 በላይ የሕግ ማሻሻያዎች ተደርገዋል ብለዋል።
ማሻሻዎቹን ተከትሎም ለበርካታ ዓመታት ለውጭ ባለሀብቶች ዝግ የነበሩ ሴክተሮችን ክፍት በማድረግ እንዲሳተፉበት ተደርጓል ነው ያሉት።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የምታደርገው ጥረት ተሳክቶ አባልነቷ ሲረጋገጥ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴውን በይበልጥ እንደሚያሳድገው አስገንዝበዋል።
በተጨማሪም በቅርቡ ወደ ተግባር የገባው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ለኢንቨስትመንት ፍሰቱ ማደግ የጎላ ሚና እንዳለው አመላክተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026