🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ):- በባለሃብቶች ይነሱ ለነበሩ ጥያቄዎች ተግባራዊ ምላሽ በመሰጠቱ የኢንቨስትመንት ፍሰቱ እንዲጨምር ማስቻሉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።
በሂደት ከተመለሱ ጥያቄዎች መካከል 14 ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች መቀየር መቻሉ አንዱ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጋር በተያያዘ ይነሱ ለነበሩ ጥያቄዎች ተግባራዊ ምላሽ መሆኑን አስረድተዋል።
እንዲሁም ከውጭ ምንዛሪ ጋር ተያይዘው ይነሱ ለነበሩ ጥያቄዎች በኢኮኖሚ ማሻሻያው መሠረት ለውጦች መገኘታቸውን ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ መዳረሻዎችን ማስፋቱ ድርጅቶች በቀላሉ ምርታቸውን ወደ ተለያዩ ሀገራት መላክ እንዲችሉ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰቱ ላይ የጎላ ሚና አበርክቷል ብለዋል።
በኮሚሽኑ የሚሰጠው የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ፈጣን፣ ግልጽና ተደራሽ የሆነ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን አመላክተዋል።
በአጠቃላይ በዘርፉ በተደረጉ ዘርፈ-ብዙ የማሻሻያ ሥራዎች በእ.ኤ.አ 2024/2025 ከ4 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ማስመዝገብ መቻሉን ለኢዜአ አረጋግጠዋል።
ኢንቨስትመንት በይበልጥ እንዲስፋፋና እንዲነቃቃ ኮሚሽኑ የተለያዩ ሥራዎች እያከናወነ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ለአብነትም ኢትዮጵያ ያላትን የኢንቨስትመንት ዕድሎች ለማስተዋወቅ የሚያስችል የአምስት ዓመት የኢንቨስትመንት ስትራቴጂ በማውጣት ወደ ሥራ መገባቱን አንስተዋል።
ቀደም ሲል የነበረውን ስትራቴጂ ወደ ኢላማ ተኮር የኢንቨስትመት ማስተዋወቅ ሥራ በመቀየር ከሌሎች ተቋማት ተግባራት ጋር በቅንጅት እየተሠራበት እንደሚገኝም ነው ኮሚሽነሩ የተናገሩት።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026