የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች በከተማ ግብርና ተጠቃሚ እየሆኑ ነው

Dec 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦በአምቦ ከተማ በከተማ ግብርና የተሰማሩ ነዋሪዎች ከምግብ ፍጆታ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናገሩ።

በአምቦ ከተማ በከተማ ግብርና የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት የተሰማሩ ነዋሪዎች በልማቱ የተመጣጠነ ምግብን ለቤተሰባቸው ከማቅረብ ባለፈ ተጨማሪ ገቢ በማግኘት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መሆኑን ተናግረዋል።


በዘርፉ ከተሰማሩ መካከል አርሶ አደር ዘርይሁን አያልቅበት፤ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት በአነስተኛ መሬታቸው ላይ ቲማቲም በማልማት ከቤተሰብ ፍጆታ አልፈው ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ገቢ አግኝተዋል።


ለገበያ ከሚያቀርቡት አትክልት ሽያጭ በመቆጠብ የወተት ላም መግዛታቸውንም ተናግረዋል።

የአትክልት ልማቱን ውጤት በየጊዜው በማየታቸው አሁን ላይ ስራውን በማስፋት ቀይ ሽንኩርትና ሌሎች የጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እያለሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ሌላው በከተማ ግብርና የተሰማሩት አቶ ዘገየ አከዋቅ በበኩላቸው፥ ወደ አትክልት ልማት ከመግባታቸው በፊት ብዙም ተጠቃሚ እንዳልነበሩ አስረድተዋል።


ከግብርና ባለሙያዎች ያገኙትን ድጋፍ ተጠቅመው በከተማ ግብርና በመሰማራት የአመጋገብ ስርዓታቸውን ለማሻሻል እና ገቢያቸውን ለማሳደግ እየተጉ ነው።

በዚህም ድንች እና ነጭ ሽንኩርት በማልማት ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።

የአምቦ ከተማ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ተወካይ አቶ ታከለ ኩምሳ እንዳሉት፤ በአምቦ ከተማ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አካል የሆነው የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ለምግብ ዋስትናና ለስራ እድል ፈጠራ እያገዘ ነው፡፡


በከተማው የበጋ መስኖ ልማት በአትክልትና ፍራፍሬ ለማልማት ከታቀደው 95 ሄክታር መሬት ውስጥ እስከ አሁን 36 ሄክታር መሬት በተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬ መሽፈኑን ተናግረዋል፡፡

የከተማው ነዋሪዎች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በመሳተፍ አትክልትና ፍራፍሬ በማምረት የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙና ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ ድጋፍና ክትትል መደረጉን አንስተዋል።

ምርታማነታቸውን ለማሳደግ የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ ግብአት በማቅረብ ለገበያ ማረጋጋት ጭምር እያገዙ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026