🔇Unmute
አምቦ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦በአምቦ ከተማ በከተማ ግብርና የተሰማሩ ነዋሪዎች ከምግብ ፍጆታ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናገሩ።
በአምቦ ከተማ በከተማ ግብርና የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት የተሰማሩ ነዋሪዎች በልማቱ የተመጣጠነ ምግብን ለቤተሰባቸው ከማቅረብ ባለፈ ተጨማሪ ገቢ በማግኘት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መሆኑን ተናግረዋል።

በዘርፉ ከተሰማሩ መካከል አርሶ አደር ዘርይሁን አያልቅበት፤ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት በአነስተኛ መሬታቸው ላይ ቲማቲም በማልማት ከቤተሰብ ፍጆታ አልፈው ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ገቢ አግኝተዋል።

ለገበያ ከሚያቀርቡት አትክልት ሽያጭ በመቆጠብ የወተት ላም መግዛታቸውንም ተናግረዋል።
የአትክልት ልማቱን ውጤት በየጊዜው በማየታቸው አሁን ላይ ስራውን በማስፋት ቀይ ሽንኩርትና ሌሎች የጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እያለሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ሌላው በከተማ ግብርና የተሰማሩት አቶ ዘገየ አከዋቅ በበኩላቸው፥ ወደ አትክልት ልማት ከመግባታቸው በፊት ብዙም ተጠቃሚ እንዳልነበሩ አስረድተዋል።

ከግብርና ባለሙያዎች ያገኙትን ድጋፍ ተጠቅመው በከተማ ግብርና በመሰማራት የአመጋገብ ስርዓታቸውን ለማሻሻል እና ገቢያቸውን ለማሳደግ እየተጉ ነው።
በዚህም ድንች እና ነጭ ሽንኩርት በማልማት ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።
የአምቦ ከተማ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ተወካይ አቶ ታከለ ኩምሳ እንዳሉት፤ በአምቦ ከተማ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አካል የሆነው የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ለምግብ ዋስትናና ለስራ እድል ፈጠራ እያገዘ ነው፡፡

በከተማው የበጋ መስኖ ልማት በአትክልትና ፍራፍሬ ለማልማት ከታቀደው 95 ሄክታር መሬት ውስጥ እስከ አሁን 36 ሄክታር መሬት በተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬ መሽፈኑን ተናግረዋል፡፡
የከተማው ነዋሪዎች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በመሳተፍ አትክልትና ፍራፍሬ በማምረት የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙና ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ ድጋፍና ክትትል መደረጉን አንስተዋል።
ምርታማነታቸውን ለማሳደግ የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ ግብአት በማቅረብ ለገበያ ማረጋጋት ጭምር እያገዙ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026