🔇Unmute
አዲስ አበባ ፤ ሕዳር 26/2018 (ኢዜአ)፡-አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ቴክኖሎጂ ተቋሙን ወደ ተሟላ የዲጂታል አገልግሎት ስርዓት የሚያሸጋግር መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የለማውን የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርዓት ዛሬ አስጀምረዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በአዲስ አበባ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን ስር ነቀል ለውጥ ከተመዘገበባቸው ዘርፎች መካከል አንዱ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ነው፡፡
በተለያዩ ዘርፎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ዘመናዊ እና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት መዘርጋቱ ነዋሪዎችን ከአላስፈላጊ የገንዘብ እና የጊዜ ብክነት ለመታደግ ማስቻሉን ጠቅሰዋል፡፡
አገልግሎቱ ይፋ ያደረገው በዲጂታል የታገዘ የአሰራር ስርዓት የተቀናጀ እና የዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችለው አስታወቀዋል፡፡
እንዲሁም ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት አይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል፡፡

አዲስ የለማው የዲጂታል ስርዓት የፋይዳ እና የነዋሪነት መታወቂያን በአንድ ላይ አቀናጅቶ የያዘ መሆኑን ጠቅሰው፤ማንኛውም ግለሰብ በስማርት ስልክ በመታገዝ ከጎግል ፕላይ ስቶር እና ከአፕል ስቶር በማውረድ መጠቀም እንደሚችል ገልጸዋል።
ቴክኖሎጂው ከተቋሙ የሚመነጩ መረጃዎችን በመሰነድ ትክክለኛ ፖሊሲ ለመቅረጽ እና እቅድ ለማዘጋጀት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን አስታውቀዋል፡፡
ዲጂታል ስርዓቱ የአዲስ አበባን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንደሚያሳድገው ጠቅሰው ከሕዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በ50 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረግ ይጀምራል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የእድገት ማቀጣጠያ መሳሪያ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ለማድረግ አያሌ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቁመው፤ በዚህም በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ ዘርፎች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡

አዲሱ ቴክኖሎጂ የተቋሙን የአገልግሎት ጥራት የሚያሳድግ እንዲሁም ብልሹ የአሰራር ስርዓትን የሚያስወግድ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዮሴፍ ንጉሴ ናቸው፡፡
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026