የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የሀገርን ብልጽግና የሚያሳልጥ ችግር ፈቺ የፈጠራ አቅም እየጎለበተ ነው

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ የሚያሳልጥ ችግር ፈቺ የፈጠራ አቅም እየጎለበተ መምጣቱን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ።

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩትና በኤስ.ኤን.ቪ ዓለም አቀፍ ድርጅት ትብብር ለ10 ቀናት የተካሄደው 6ኛው ሀገር አቀፍ ''ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር'' ተጠናቋል።


በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ፤ በውድድሩ ከተሳተፉ 251 የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ተወዳዳሪዎች ውስጥ አንድ መቶ የሚሆኑት ለሽልማት በቅተዋል ብለዋል።

''ማሰልጠን፣ መሸለምና ማብቃት” የሚል መሪ ሃሳብ በተሰጠው ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር የግብርና፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂና ሌሎች ዘርፎች ምርታማነትን የሚያሻሽሉ የፈጠራ ስራዎች መቅረባቸውን ገልጸዋል።

አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎችንም በመረጃ ቋት በማደራጀት በኢንተርፕርነርሽፕ ስታርት አፕ ፈጠራ የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት እያሳደገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ የሚያሳልጥ ችግር ፈቺ የፈጠራ አቅም እየጎለበተ ነው ያሉት አቶ ሰለሞን፤ በፈጠራና ፍጥነት በዕውቀትና ክህሎት የበለጸጉ ዜጎችን የማፍራት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን (ዶ/ር)፤ ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር የኢትዮጵያዊንን ዕምቅ የፈጠራ ክህሎት በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል።

በቀጣይም የኢትዮጵያዊያን የፈጠራ ክህሎት ለሀገር ዕድገትና ብልጽግና አጋዥ የሚሆንበትን የማበረታቻ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

የፈጠራ ባለሙያዎችም የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች በትጋት በማለፍ ለበለጠ ውጤት እንዲበቁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ቦሩ ካና በበኩላቸው፤ ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር ውጤታማ ስታርት አፖችን ማፍራት እያስቻለ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በኤስ.ኤን.ቪ ዓለም አቀፍ ድርጅት የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ጁሊ ግርሃም፤ በውድድሩ የተመረጡ የፈጠራ ስራዎች ወደ ስራ እንዲገቡ በጋራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

የፈጠራ ስራዎች ለኢትዮጵያ እድገት ማዕከል ሆነው እንዲቀጥሉ በትብብር እንሰራለን ብለዋል።

በፈጠራ ውድድሩ በግብርና ፣ በጤና ፣ በቴክኖሎጂና ሌሎች ዘርፎችን የሚደግፉ የፈጠራ ስራዎች ተሸላሚ ሆነዋል።

ከእነዚህም መካከል አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የፈጠራ ባለሙያዎች የፈጠራ ስራቸው ለተኪ ምርት፣ ለግብርና ምርት ጥራት እንዲሁም ለአካል ጉዳተኞች ባማከለ መልኩ የሚኖረውን ጠቀሜታ ገልጸዋል።

በቀጣይም የፈጠራ ስራቸውን በስፋት ወደ ገበያ ለማስገባትና የስራ ዕድልን ለማስፋፋት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026