🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ የሚያሳልጥ ችግር ፈቺ የፈጠራ አቅም እየጎለበተ መምጣቱን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩትና በኤስ.ኤን.ቪ ዓለም አቀፍ ድርጅት ትብብር ለ10 ቀናት የተካሄደው 6ኛው ሀገር አቀፍ ''ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር'' ተጠናቋል።

በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ፤ በውድድሩ ከተሳተፉ 251 የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ተወዳዳሪዎች ውስጥ አንድ መቶ የሚሆኑት ለሽልማት በቅተዋል ብለዋል።
''ማሰልጠን፣ መሸለምና ማብቃት” የሚል መሪ ሃሳብ በተሰጠው ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር የግብርና፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂና ሌሎች ዘርፎች ምርታማነትን የሚያሻሽሉ የፈጠራ ስራዎች መቅረባቸውን ገልጸዋል።
አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎችንም በመረጃ ቋት በማደራጀት በኢንተርፕርነርሽፕ ስታርት አፕ ፈጠራ የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት እያሳደገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ የሚያሳልጥ ችግር ፈቺ የፈጠራ አቅም እየጎለበተ ነው ያሉት አቶ ሰለሞን፤ በፈጠራና ፍጥነት በዕውቀትና ክህሎት የበለጸጉ ዜጎችን የማፍራት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን (ዶ/ር)፤ ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር የኢትዮጵያዊንን ዕምቅ የፈጠራ ክህሎት በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል።
በቀጣይም የኢትዮጵያዊያን የፈጠራ ክህሎት ለሀገር ዕድገትና ብልጽግና አጋዥ የሚሆንበትን የማበረታቻ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የፈጠራ ባለሙያዎችም የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች በትጋት በማለፍ ለበለጠ ውጤት እንዲበቁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ቦሩ ካና በበኩላቸው፤ ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር ውጤታማ ስታርት አፖችን ማፍራት እያስቻለ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በኤስ.ኤን.ቪ ዓለም አቀፍ ድርጅት የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ጁሊ ግርሃም፤ በውድድሩ የተመረጡ የፈጠራ ስራዎች ወደ ስራ እንዲገቡ በጋራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
የፈጠራ ስራዎች ለኢትዮጵያ እድገት ማዕከል ሆነው እንዲቀጥሉ በትብብር እንሰራለን ብለዋል።
በፈጠራ ውድድሩ በግብርና ፣ በጤና ፣ በቴክኖሎጂና ሌሎች ዘርፎችን የሚደግፉ የፈጠራ ስራዎች ተሸላሚ ሆነዋል።
ከእነዚህም መካከል አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የፈጠራ ባለሙያዎች የፈጠራ ስራቸው ለተኪ ምርት፣ ለግብርና ምርት ጥራት እንዲሁም ለአካል ጉዳተኞች ባማከለ መልኩ የሚኖረውን ጠቀሜታ ገልጸዋል።
በቀጣይም የፈጠራ ስራቸውን በስፋት ወደ ገበያ ለማስገባትና የስራ ዕድልን ለማስፋፋት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026