🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፦በመዲናዋ የኮሪደር ልማት ስራ ላይ በመሠማራት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችውን ከማረጋገጥ ባለፈ ለሌሎችም የሥራ ዕድል እየፈጠሩ መሆኑን በከተማ ውበት፣ አረንጓዴ ልማትና ችግኝ አቅርቦት የተሰማሩ ማህበራት ገለጹ።
በአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ለነዋሪዎችም ሆነ ለጎብኝዎች ምቹና ሳቢ የሆኑ በርካታ መዝናኛዎች፣ ፓርኮችና የመንገድ አካፋዮች ተገንብተው ለከተማዋ ልዩ ገጽታ እየፈጠሩ ይገኛሉ።

የኮሪደር ልማቱ መዲናዋን ውብና ጽዱ ከማድረግ ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉም ይነገራል።
ኢዜአ ያነጋገራቸው በመዲናዋ በከተማ ውበት፣ አረንጓዴ ልማትና ችግኝ አቅርቦት ላይ የተሰማሩ ማህበራት በስራቸው ውጤታማ ከመሆን ባለፈ ለሌሎችም የሥራ ዕድል መፍጠር መቻላቸውን ተናግረዋል።
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ነዋሪ የሆኑት ቀሲስ አዱኛ ጥጋቤ፤ በግልና በማህበር የተለያዩ ችግኞችን በማፍላት ለገበያ እያቀረቡ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዚህም ለውበትና ለአረንጓዴ ልማት አስተዋፅኦ እያበረከቱ መሆኑን ገልፀው ማህበራቸው ከፍተኛ ገቢ እያመነጨ ከመሆኑም በላይ ለ40 ወጣቶች ጊዜያዊና ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል።
በከተማ ውበትና አረንጓዴ እንክብካቤ ዘርፍ የተሰማሩት የውብዓለምና መሀመድ ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ውብዓለም ልባሴ፤ የኮሪደር ልማት የሥራ ዕድል ይዞላቸው እንደመጣ አስረድተዋል።

ከዚህ ቀደም ሥራ ስላልነበራቸው የባለቤታቸውን እጅ እየጠበቁ ይኖሩ እንደነበር በማውሳት፥ አሁን ላይ በተፈጠረላቸው የሥራ ዕድል በመንገድ አካፋዮች የተተከሉ እፅዕዋትን በመንከባከብ ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተዋል።
የአዲስ አበባ የስራና ክህሎት ቢሮ የስራ ስምሪት አገልግሎት ዳይሬክተር ሰብሀዲን ሱልጣን፤ ለስራ አጥ ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
መዲናዋን እንደ ስሟ ውብና ስማርት ሲቲ ለማድረግ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ለበርካታ ስራ አጥ ዜጎች ምቹ የስራ ዕድል ይዞ መምጣቱን ተናግረዋል።

በዚህም 560 ማህበራት በከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ዘርፍ ተሰማርተው ለከተማዋ ውበትና ሳቢነት የድርሻቸውን በመወጣት ላይ ይገኛሉ ነው ያሉት።
በመዲናዋ እየተመዘገበ ላለው ፈጣን ልማትና እድገት ማህበራት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ በሥራ ዕድልም ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ አመላክተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026