የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢንዱስትሪዎች የሚፈልጉትን ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት የተሰጠው ትኩረት ውጤት እያመጣ ነው

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፦የአካባቢን ፀጋ መሰረት ባደረገ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንዱስትሪዎች የሚፈልጉትን ብቁ የሰው ኃይል የማፍራት ሥራ ውጤት እያመጣ መሆኑን የተለያዩ የክልል የቢሮ ኃላፊዎች ገለጹ።

ኃላፊዎቹ እንዳሉት፡ በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች ትስስር በመፍጠር ሠልጣኞች የተግባር ትምህርት በአግባቡ እንዲያገኙና በፍጥነት ወደ ሥራው ዓለም እንዲቀላቀሉ እያስቻለ ነው።

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሮቤል ጌታቸው፤ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናው ገበያን መሰረት አድርጎ መስጠት መጀመሩ ሠልጣኞች በሥራ ገበያው ያላቸውን ተወዳዳሪነት ማሳደጉን ገልጸዋል።


ለሥራ ዕድል ፈጠራ ትልቅ ሚና እንዳለው በማንሳትም፥ ባለፈው ዓመት ብቻ ለ19 ሺህ ዜጎች በዚህ ዓመት ደግሞ እስካሁን ለ4 ሺህ 700 ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር መቻሉን ነው የገለጹት።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሙስጠፋ ኢሳ በበኩላቸው፤ በቴክኒክና ሙያ እየተሰጠ ያለው የአጫጭር እና መደበኛ ስልጠና የሥራ ፈጣሪነት አቅምን እያጎለበተ ነው ብለዋል።


ጥራት ያለው ስልጠና በመስጠት ገበያው የሚፈልገውን የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ ውጤት ማምጣት መቻሉን አመልክተዋል።

የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን አቅም ይበልጥ ለማሳደግ የተሻለ ጥራት ያለው ስልጠና የመስጠት ሰፋፊ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ያሉት ደግሞ የኦሮሚያ ክልል ሥራ እድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ኤባ ገርባ ናቸው።


በዚህም በከተማም ሆነ በገጠር እየተፈጠሩ ያሉ የልማት አቅሞች ለቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች ሰፊ የሥራ እድል እየፈጠሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የአማራ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አማረ አለሙ፤ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሪፎርም ኮሌጆች ተልእኳቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ከማድረግ ባለፈ በቂ ክህሎት የተላበሰ ዜጋ ለማፍራት እያስቻለ ነው ብለዋል።


ስልጠናዎች በየአካባቢው ያለው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚፈልገውን የሰው ኃይል መሰረት አድርገው እንዲሰጡ መደረጉ ውጤት እያመጣ መሆኑን አብራርተዋል።

የአፋር ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አህመድ ኢብራሂም፤ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በየአካባቢው ያለውን ፀጋ መሰረት አድርገው ስልጠና መስጠታቸው በሥራ ዕድል ፈጠራና በኢኮኖሚ ለውጥ እንዲመጣ አስችለዋል ነው ያሉት።


የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ዜጎች በሥራና በፈጠራ ውጤት ሃብት መፍጠር እንዲችሉ እያደረገ ነው ያሉት ደግሞ የሲዳማ ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሀገረጽዮን አበበ ናቸው ።


በክልሉ ሰልጣኞች ከኢንዱስትሪዎች ጋር ትስስር እንዲፈጥሩ ከማድረግ አንፃር ስኬታማ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026