🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 1/2018(ኢዜአ)፡- እየተከናወኑ ያሉ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ ዐቅም ለመሸፈን የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአማራ ክልል አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ።
በክልሉ የነበረውን ሥር የሰደደ የተረጂነት አስተሳሰብና ተግባር ለመቅረፍ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር ምክክሮች መደረጋቸውን የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ሠርክአዲስ አታሌ ለኢዜአ ተናግረዋል።
ይህን ተከትሎም ከጠባቂነት መውጣትና እርስ በርስ የመደጋገፍ ዐቅምን ለማዳበር መግባባት ላይ መደረሱን ጠቁመው፤ ይህን በይበልጥ ለማስፋትና ለማጠናከር ቀጣይነት ያላቸው ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል።
እንደመንግስት ከሚከናወኑ ተግባራት ባለፈ መረዳትን ባህል እንዳሆን የሚያስችሉ እና ህብረተሰቡ የምግብ ሉዓላዊነቱን እንዲያረጋግጥ የማድረግ ስራ በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት።
ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ ዐቅም ለመሸፈን ማምረት ቁልፍ ጉዳይ መሆኑንም ምክትል ኮሚሽነሯ አስገንዝበዋል።
እስካሁን በተሠሩ ሥራዎች አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቁመው፤ በዚህ ከቀጠልን ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ መሸፈን የሚያስችል ዐቅም እናዳብራለን ሲሉም ተናግረዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026