የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ ዐቅም ለመሸፈን የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ኮሚሽኑ

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 1/2018(ኢዜአ)፡- እየተከናወኑ ያሉ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ ዐቅም ለመሸፈን የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአማራ ክልል አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ።

በክልሉ የነበረውን ሥር የሰደደ የተረጂነት አስተሳሰብና ተግባር ለመቅረፍ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር ምክክሮች መደረጋቸውን የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ሠርክአዲስ አታሌ ለኢዜአ ተናግረዋል።

ይህን ተከትሎም ከጠባቂነት መውጣትና እርስ በርስ የመደጋገፍ ዐቅምን ለማዳበር መግባባት ላይ መደረሱን ጠቁመው፤ ይህን በይበልጥ ለማስፋትና ለማጠናከር ቀጣይነት ያላቸው ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል።

እንደመንግስት ከሚከናወኑ ተግባራት ባለፈ መረዳትን ባህል እንዳሆን የሚያስችሉ እና ህብረተሰቡ የምግብ ሉዓላዊነቱን እንዲያረጋግጥ የማድረግ ስራ በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት።

ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ ዐቅም ለመሸፈን ማምረት ቁልፍ ጉዳይ መሆኑንም ምክትል ኮሚሽነሯ አስገንዝበዋል።

እስካሁን በተሠሩ ሥራዎች አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቁመው፤ በዚህ ከቀጠልን ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ መሸፈን የሚያስችል ዐቅም እናዳብራለን ሲሉም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025