🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 1/2018(ኢዜአ)፡- እየተከናወኑ ያሉ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ ዐቅም ለመሸፈን የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአማራ ክልል አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ።
በክልሉ የነበረውን ሥር የሰደደ የተረጂነት አስተሳሰብና ተግባር ለመቅረፍ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር ምክክሮች መደረጋቸውን የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ሠርክአዲስ አታሌ ለኢዜአ ተናግረዋል።
ይህን ተከትሎም ከጠባቂነት መውጣትና እርስ በርስ የመደጋገፍ ዐቅምን ለማዳበር መግባባት ላይ መደረሱን ጠቁመው፤ ይህን በይበልጥ ለማስፋትና ለማጠናከር ቀጣይነት ያላቸው ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል።
እንደመንግስት ከሚከናወኑ ተግባራት ባለፈ መረዳትን ባህል እንዳሆን የሚያስችሉ እና ህብረተሰቡ የምግብ ሉዓላዊነቱን እንዲያረጋግጥ የማድረግ ስራ በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት።
ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ ዐቅም ለመሸፈን ማምረት ቁልፍ ጉዳይ መሆኑንም ምክትል ኮሚሽነሯ አስገንዝበዋል።
እስካሁን በተሠሩ ሥራዎች አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቁመው፤ በዚህ ከቀጠልን ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ መሸፈን የሚያስችል ዐቅም እናዳብራለን ሲሉም ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025