የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ በዲጂታል አሰራር የተደገፉ አገልግሎቶችን በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ፤ታህሳስ 25/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዲጂታል አሰራር የተደገፉ አገልግሎቶችን በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደረጉ ተገለጸ፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማ በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።

በመድረኩ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በክልሉ ዲጂታል 2030ን በማሳካት የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።


''ከዲጂታል ቴክኖሎጂ ውጭ የሚታሰብ መንግስታዊ አገልግሎት አይኖርም'' ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፥ ወረቀት አልባ አገልግሎቶችን በማስፋፋት ህዝቡን ከእንግልትና ከአላስፈላጊ ወጪ ለማዳን በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

ከሁሉም በላይ በክልሉ በዲጂታል አሰራር የተደገፉ አገልግሎቶችን በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቷል ነው ያሉት።

የፋይዳ መታወቂያ ዜጎችን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር በማስተሳሰር ህይወትን በእጅጉ የሚያቀል በመሆኑ ዜጎች የዚሁ ትሩፋት ተጠቃሚ ለመሆን ፋይዳ መታወቂያ መያዝ እንዳለባቸውም ገልጸዋል።


የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ ቦጋለ ቦሼ (ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን ለማሳካት በተደረጉ ጥረቶች ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል፡፡

በክልሉ የተጀመሩ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እና የዲጂታል መታወቂያ ስራዎች ጉልህ ፋይዳ አላቸው ብለዋል።

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ዕቅድ ለማሳካት ክልሉ ድርሻውን እንዲጫወት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሠራም ጠቁመዋል።

በመድረኩ የክልልና የዞኖች እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ታድመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025