የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ በዲጂታል አሰራር የተደገፉ አገልግሎቶችን በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ፤ታህሳስ 25/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዲጂታል አሰራር የተደገፉ አገልግሎቶችን በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደረጉ ተገለጸ፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማ በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።

በመድረኩ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በክልሉ ዲጂታል 2030ን በማሳካት የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።


''ከዲጂታል ቴክኖሎጂ ውጭ የሚታሰብ መንግስታዊ አገልግሎት አይኖርም'' ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፥ ወረቀት አልባ አገልግሎቶችን በማስፋፋት ህዝቡን ከእንግልትና ከአላስፈላጊ ወጪ ለማዳን በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

ከሁሉም በላይ በክልሉ በዲጂታል አሰራር የተደገፉ አገልግሎቶችን በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቷል ነው ያሉት።

የፋይዳ መታወቂያ ዜጎችን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር በማስተሳሰር ህይወትን በእጅጉ የሚያቀል በመሆኑ ዜጎች የዚሁ ትሩፋት ተጠቃሚ ለመሆን ፋይዳ መታወቂያ መያዝ እንዳለባቸውም ገልጸዋል።


የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ ቦጋለ ቦሼ (ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን ለማሳካት በተደረጉ ጥረቶች ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል፡፡

በክልሉ የተጀመሩ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እና የዲጂታል መታወቂያ ስራዎች ጉልህ ፋይዳ አላቸው ብለዋል።

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ዕቅድ ለማሳካት ክልሉ ድርሻውን እንዲጫወት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሠራም ጠቁመዋል።

በመድረኩ የክልልና የዞኖች እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ታድመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026