🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 25/2018(ኢዜአ)፦ የግብይት ሥርዓቱን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።
በሚኒስትሩ የተመራ የልዑክ ቡድን በከተማዋ ተዘዋውሮ የንግድ እንቅስቃሴ ቅኝት አድርጓል።

በዚሁ ጊዜ ተቋማቸው በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የተያዙ ግቦች እንዲሳኩ የድርሻውን እየተወጣ ነው ብለዋል።
የወጪ ንግድ ኮንትራትና የፍቃድ አሰጣጡን ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል ሥርዓት መቀየሩን ገልጸው፣ የዲጂታል ግብይት እንዲሳለጥም ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ለአብነትም በአንድ ወር ብቻ ጤፍ በዘመን ገበያ የ53 ሚሊዮን ብር ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል።
መንግስት የዲጂታል ግብይትን ለማሳለጥ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን ወደ ዲጂታል ግብይት እንዲገቡ ይደረጋል ብለዋል።
እንደ ሚኒስትሩ ማብራሪያ በቁም እንሰሳት ንግድ ላይ የደላላ ጣልቃገብነት በመቀነስና አሰራሩን በማዘመን የተሻለ አፈጻጸም ተመዝግቧል።

የቁም እንስሳት የግብይት ማዕከላትን በማስፋት የግብይቱን ሥርዓት ግልጽና ዘመናዊ መደረጉን ገልጸው፤ከቁም እንስሳት ወጪ ንግዱ ገቢ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።
በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከቁም እንስሳት ወጪ ንግድ ከ30 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱንም ነው የተናገሩት።
በ2018 በጀት ዓመት ከቁም እንስሳት ወጪ ንግድ 70 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዷል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026