🔇Unmute
ጅግጅጋ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ኢትዮጵያ ለያዘችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬታማነት ቁልፍ ሚናን የሚጫወት መሆኑን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ ዮዳሄ አርአያስለሴ ገለጹ።
የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም 2ኛው ዙር "ፋይዳ ለኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሐሳብ የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ በጅግጅጋ ከተማ ተካሄዷል።

በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ ዮዳሄ አርአያስለሴ እንደገለጹት፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ኢትዮጵያ ለያዘችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬታማነትም ቁልፍ ሚናን የሚጫወት ነው።
ዜጎች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን በመውሰድ የዜግነት መብታቸውን መጠቀም እንዳለባቸውም ጥሪ አስተላልፈዋል።
የሱማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን፤ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ለሀገር ዕድገት ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸው በክልሉ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡

ለዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አስፈላጊ በመሆኑ ሁሉም ዜጋ እንዲወስድ ሃላፊው አሳስበዋል።
የዛሬው የሩጫ ውድድርም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሂደትን ከማነቃቃት ባለፈ በስፖርት ተወዳዳሪ ወጣቶችን ለማፍራት ትልቅ ዕድል መሆኑን አንስተዋል።
በጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሩ የክልሉ አመራሮች፣ አትሌት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አትሌቶች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሁም የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026