የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ እና ኦማን በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ኦማን የአፍሪካ ቀንድን ጨምሮ በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በትብብር እንደሚሰሩ አስታወቁ።


የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና የኦማን የፖለቲካ ምክክር በአዲስ አበባ ተካሄዷል።


የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ኢትዮጵያ እና ኦማን ኢኮኖሚና ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ሀገራቱ የሁለትዮሽ ትስስራቸውን ማጠናከር የሚችሉባቸው በርካታ ዘርፎች እንዳሉ በምክክሩ ላይ መነሳቱን የፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ ዘገባ ያመለክታል።


ቱሪዝም እና የሀገራቱ ዜጎች የጉብኝት ልውውጥ የሀገራቱን ትብብር ለማጎልበት እንደሚያስችል ተናግረዋል።


ሀገራቱ በአፍሪካ ቀንድ እና የባህረ ሰላጤው ቀጣና ጉዳይ ላይ ያላቸውን ግንነት ለማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በስፋት መምከራቸውን ጠቁመዋል።


ኢትዮጵያ እና ኦማን ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶችን ለማድረግ እንዲሁም በቱሪዝም እና ንግድ ዘርፍ ያላቸውን ትስስር ለማሳደግ ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ነው ሚኒስትር ዴኤታው የጠቆሙት።


የኦማን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሼህ ከሊፋ ቢን አሊ አል ሃርቲ በኢትዮጵያ ያደረጉት የስራ ጉብኝት አላማ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብርን ማጠናከር መሆኑን ለፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ ገልጸዋል።


በጉብኝቱ ኦማን እና ኢትዮጵያ በሁለትዮሽ እና በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደተስማሙ ተናግረዋል።


ስምምነት ከተደረሰባቸው ጉዳዮች መካከል የአፍሪካ ቀንድ እና ባህረ ሰላጤ ቀጣና ላይ በጋራ መስራት እንደሚገኝበት ተናግረዋል።


ኦማን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደሆነችም አረጋግጠዋል።


ሁለቱ ወገኖች የሁለትዮሽ የፖለቲካ ምክክር በማድረግ የሁለትዮሽ ትብብርን ለማሳደግ ፣በቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ቅንጅትን ለማጠናከር የጋራ የመግባቢያ ስምምነት በምክክሩ ወቅት ተፈራርመዋል።


የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፖለቲካ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ሼክ ካሊፋ ቢን አሊ አል ሀርቲ ከውጭ ጉደይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋር የሁለት ሀገራት ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ እና በጋራ ቀጣናዊና የሰላም እንዲሁም የጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025