የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ እና ኦማን በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ኦማን የአፍሪካ ቀንድን ጨምሮ በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በትብብር እንደሚሰሩ አስታወቁ።


የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና የኦማን የፖለቲካ ምክክር በአዲስ አበባ ተካሄዷል።


የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ኢትዮጵያ እና ኦማን ኢኮኖሚና ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ሀገራቱ የሁለትዮሽ ትስስራቸውን ማጠናከር የሚችሉባቸው በርካታ ዘርፎች እንዳሉ በምክክሩ ላይ መነሳቱን የፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ ዘገባ ያመለክታል።


ቱሪዝም እና የሀገራቱ ዜጎች የጉብኝት ልውውጥ የሀገራቱን ትብብር ለማጎልበት እንደሚያስችል ተናግረዋል።


ሀገራቱ በአፍሪካ ቀንድ እና የባህረ ሰላጤው ቀጣና ጉዳይ ላይ ያላቸውን ግንነት ለማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በስፋት መምከራቸውን ጠቁመዋል።


ኢትዮጵያ እና ኦማን ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶችን ለማድረግ እንዲሁም በቱሪዝም እና ንግድ ዘርፍ ያላቸውን ትስስር ለማሳደግ ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ነው ሚኒስትር ዴኤታው የጠቆሙት።


የኦማን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሼህ ከሊፋ ቢን አሊ አል ሃርቲ በኢትዮጵያ ያደረጉት የስራ ጉብኝት አላማ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብርን ማጠናከር መሆኑን ለፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ ገልጸዋል።


በጉብኝቱ ኦማን እና ኢትዮጵያ በሁለትዮሽ እና በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደተስማሙ ተናግረዋል።


ስምምነት ከተደረሰባቸው ጉዳዮች መካከል የአፍሪካ ቀንድ እና ባህረ ሰላጤ ቀጣና ላይ በጋራ መስራት እንደሚገኝበት ተናግረዋል።


ኦማን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደሆነችም አረጋግጠዋል።


ሁለቱ ወገኖች የሁለትዮሽ የፖለቲካ ምክክር በማድረግ የሁለትዮሽ ትብብርን ለማሳደግ ፣በቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ቅንጅትን ለማጠናከር የጋራ የመግባቢያ ስምምነት በምክክሩ ወቅት ተፈራርመዋል።


የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፖለቲካ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ሼክ ካሊፋ ቢን አሊ አል ሀርቲ ከውጭ ጉደይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋር የሁለት ሀገራት ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ እና በጋራ ቀጣናዊና የሰላም እንዲሁም የጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026