የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኮሪደር ልማት ስራው የነዋሪው የልማት ተነሳሽነት እንዲጎለብት አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦የጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራ ለከተማዋ ወጣቶች ሰፊ የስራ እድል ከመፍጠር ባሻገር የነዋሪው የልማት ተነሳሽነት እንዲጎለብት አስተዋጽኦ እያበረከተመሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ፡፡

የጎንደር ከተማ ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራ አካል የኮንክሪት አስፓልት መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑ እና በመጪው የጥምቀት በዓል በይፋ ተመርቆ ስራ እንደሚጀምር ታውቋል፡፡


የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በከተማዋ የሚከናወነው ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ የህዝቡን ተሳትፎ በማቀናጀት የከተማዋን ገጽታ ለመቀየርና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን በሚያሳልጥ መልኩ እየተካሄደ ነው፡፡


የሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማቱ የእግረኞችና የብስክሌት መንገዶችን ጨምሮ ዘመናዊ መናፈሻዎችና ፓርኮችን እንዲሁም አረንጓዴ ስፍራዎችን በማካተት መገንባቱን አስረድተዋል፡፡

የዚሁ ስራ አካል የሆነው የኮንክሪት አስፓልት 8 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር መንገድ ግንባታን በማፋጠን ለጥምቀት በዓል በማጠናቀቅ ለትራፊክ ክፍት ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡


በተጨማሪም ኮሪደሩ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን፣ ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራቶችንና ስማርት የመጸዳጃ ቤቶችን ያካተተ ሲሆን ከተማዋ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንድትሆን ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ነው ብለዋል፡፡

የኮሪደር ልማት ስራው ለከተማው ወጣቶች ሰፊ የስራ እድል መፍጠሩን ጠቁመው በህዝቡ ዘንድም የልማት ተነሳሽነት እንዲጎለብት የላቀ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል፡፡

ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራ 12 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትርን የሸፈነ ሲሆን በመጪው ጥር ወር በታላቅ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ስርዓት በሚከበረው የጥምቀት በዓል በይፋ ተመርቆ ስራ እንደሚጀምር ገልጸዋል፡፡


የከተማውን የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ይበልጥ በማነቃቃት በኩል የኮሪደር ልማት ስራው ትልቅ ተስፋን የሰነቀና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳውም የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ከፍተኛ ወጪ ተደርጎባቸው የተገነቡት ግዙፍ መሰረተ ልማቶች ለህዝቡ የዘመናት የመልማት ጥያቄ ምላሽ በመስጠት የከተማዋን ዳግም ትንሳኤ ያበሰሩ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶች ናቸው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026