የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለው የኢኮኖሚ ትብብር ቀጣይነት ባለው መልኩ እያደገ በመምጣቱ በሁለቱ ሀገራት ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስፋፋ አድርጓል

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለው የኢኮኖሚ ትብብር ቀጣይነት ባለው መልኩ እያደገ በመምጣቱ በሁለቱ ሀገራት ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰትን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስፋፋ ማድረጉን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ፡፡

የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የኢትዮጵያ እና ቻይናን ግንኙነት በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል።

ሙሉ መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል።

ሁለንተናዊ ትብብር የኢትዮ-ቻይና አጋርነት የጀርባ አጥንት ነው

የኢትዮ-ቻይና የንግድ ልውውጡ ከ13 ቢሊዮን ዶላር በልጧል።

የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ም

በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለው የኢኮኖሚ ትብብር ቀጣይነት ባለው መልኩ እያደገ በመምጣቱ በሁለቱ ሀገራት ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰትን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስፋፋ አድርጓል፡፡

በዚህም የሁለትዮሽ የንግድ ለውውጥ ከ13 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የበለጠ ሲሆን፣ ይህም ቻይና ኢትዮጵያን ዋነኛ የንግድ አጋር በማድረግ ግንኙነቷን እያጠናከረች መሆኑን ማሳያ ነው፡፡ ኢትዮጵያም ከቻይና የምታስገባው ምርት በተጠናቀቀው ዓመት መጀመሪያ ላይ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን በመጋቢት ወር ብቻ 1.57 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ደርሷል፡፡ ይህም ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 22% ጭማሪ አሳይቷል።

የውጭ ቀጥተኛ የኢንቨስትመንት ፍሰትም ጠንካራ ሆኖ የቀጠለ ሲሆን፣ ቻይና በማኑፋክቸሪንግ፣ በመንገድና ሕንጻ ፕሮጀክት ግንባታዎች ላይ በመሰማራት ግንባር ቀደም ሀገር ሆና እየሰራች ነዉ፡፡

የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞን የሚያፋጥኑ የመሠረተ ልማትና የፋይናንስ ተደራሽነት ማስፋፋት በተለይ ከባቡር ሐዲድ ዝርጋታ፣ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች እስከ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ድረስ የተገኙ ስኬቶች የሁለቱን ሀገራት የኢኮኖሚ አጋርነትን አጠናክሯል፡፡

የኢኮኖሚ ትብብር የዚህ አጋርነት የጀርባ አጥንት ሲሆን፣ በየካቲት 2017 በአዲስ አበባ የተካሄደው የኢትዮ-ቻይና የኢኮኖሚ እና የንግድ ልዉዉጥ መድረክ በኢንቨስትመንት፣ በንግድ እና በአቅርቦት ሰንሰለቶች ላይ ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ ኢንዲጠናክር አድርጓል፡፡

ኢትዮጵያ በዚሁ ዓመት ወደ አዲሱ የዓለም የኢኮኖሚ ጥምረት፣ BRICS+ መቀላቀሏ ለዘመናዊነት እና የቻይናን ጨምሮ ለአለም አቀፍ ገበያዎች ተደራሽ የመሆን እድሎችን አስፍቷል፡፡

ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣዉ የሁለትዮሽ ኢኮኖሚ አጋርነት ለሁለቱም ሀገራት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለዉ ነው፡፡ የኢትዮጵያን የዲጂታል ራዕይ ወሳኝ የሆኑ የካፒታል፣ የቴክኖሎጂ እና የገበያዎች መዳረሻ እንዲትሆን እድል የሚያሰፋ ሲሆን፣ ለቻይና ደግሞ ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ በር ሆና ታገለግላለች፡፡ በተለይ ከቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ ጋር በማጣጣም የቻይና የረጅም ጊዜ የጋራ ልማት ራዕይን እዉን ያደርጋል፡፡

ከዚህ አንጻር የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ፣ የፈረንጆቹን የ2026 አዲሱን ዓመት የውጭ አገር ጉብኝታቸውን በአፍሪካ ለመጀመር ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡

ይህ ጉብኝት ቻይና የዓመቱን የመጀመሪያ የዲፕሎማሲ ጉዞ በአፍሪካ አገራት የመጀመር የ36 ዓመታት ረጅም ታሪክ አካል ነዉ፡፡ ጉብኝቱ በተለይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ሶማሊያ፣ ታንዛኒያ እና ሌሶቶን የሚያካትት ሲሆን ይህም ቻይና ለአፍሪካ ቀንድና ለቀሪው የአፍሪካ አገራት የምትሰጠውን ትኩረት ከማመላከት ባሻገር የኢትዮጵያ-ቻይና ግንኙነት ለአፍሪካ-እስያ ትብብር የማዕዘን ድንጋይ ሆኖ እንዲቀጥል የጎላ ድርሻ አለዉ፡፡

ሁለቱ ሀገራት በዛሬው ዕለት በኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ መሠረተ ልማት፣ የኃይል አቅርቦት እና ትራንስፖርት ብሎም አዲስ በመፈጠር ላይ ባሉ እንደ ኢ-ኮሜርስ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና አረንጓዴ ኃይል ልማት ላይ ትብብራችንን ለማጠናከር ተወያይተዋል።

በአጠቃላይ የቻይና ዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ጉብኝት፣ በኢትዮጵያና በቻይና መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ስልታዊ የኢኮኖሚ ትብብር አጋርነት ይበልጥ እንደሚያጠናክረውና በቤጂንግ በተካሄደው የቻይና-አፍሪካ ትብብር ፎረም (FOCAC) የተመዘገቡ ስምምነቶችን ወደ ተግባር ለመቀየር ፋይዳው የጎላ እንደሆነ ያመላክታል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025