የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኦሮሚያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በ27 ማዕከሎች ላይ እየተሰጠ ነው

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በ27 ማዕከሎች ላይ እየተሰጠ መሆኑን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ገለጸ።

መንግስት በተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ በህዝቡ ይነሳ የነበረውን ቅሬታ ለመፍታት በርካታ ውጤታማ ስራዎች እያከናወነ ሲሆን ከእነዚህ መካከል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ይገኝበታል።

በአዲስ አበባ ከተማ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ወደ ክልሎችም ተስፋፍቶ የመሬት፣ የገቢ እና ሌሎች አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል እየተሰጡ መሆኑ ይታወቃል።

የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ሃይሉ አዱኛ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ በክልሉ መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በክልሉ በሸገር፣ በአዳማ፣ በቢሾፍቱ፣ በጅማ እና በሻሸመኔ ከተሞች የተጀመረው አገልግሎቱ በዚህ ወቅት ወደ 27 ማዕከሎች ማስፋት መቻሉን ተናግረዋል።


አገልግሎቱ በተለይም የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ከመመለስ እና ብልሹ አሰራሮችን ከማስቀረት ጋር በተገናኘ ህዝቡ ለረጅም ጊዜ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እያገዘ መሆኑን ገልጸዋል።

ማዕከላቱ በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ መስኮት መስጠት ማስቻሉ ብቻ ሳይሆን ተገልጋዩ በአጭር ጊዜ ጉዳዩን እንዲፈጽም እያስቻሉ ነው ብለዋል።

በቀጣይም በተማ አስተዳደር ደረጃ ያሉትን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ወደ ክፍለ ከተሞች የማውረድ ስራ በትኩረት እንደሚከናወንም ተናግረዋል።

በክልሉ በየደረጃው ያለው አመራርም ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር የተያያዙ ችግሮች እንዲቀረፉ ከሌሎች የልማት ስራዎች እኩል ትኩረት ሰጥቶ እየተረባረበ መሆኑን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026