የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በመዲናዋ የተገነቡ የልማት ስራዎችን የመጠበቅና የመንከባከብ ሃላፊነት የሁላችንም ነው-ነዋሪዎች

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የተገነቡ የወንዝ ዳርቻና የኮሪደር ልማቶችን የመጠበቅና የመንከባከብ ሃላፊነት የሁላችንም ነው ሲሉ የመዲናዋ ነዋሪዎች ገለጹ።

አዲስ አበባን ዘመናዊ ለነዋሪዎቿ ምቹ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለማድረግ እየተከናወኑ ከሚገኙ ስራዎች መካከል የወንዝ ዳርቻ ልማት አንዱ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በቅርቡ የቀበናና ግንፍሌ ወንዝ ዳርቻ ልማት ሂደትን በተመለከቱበት ወቅት እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቶቹ ወንዞችና ዳርቻዎቻቸውን ከስጋትና ከብክለት ነጻ በማድረግ ስነ-ምህዳሯን የጠበቀች፤ ውብና ፅዱ ከተማ ለመፍጠር እያስቻሉ ነው፡፡


በከተማዋ ተረስተው የነበሩና ከልማት ተገልለው የቆዩ የወንዝ ዳርቻዎች ዛሬ ላይ የብዙዎች አይን ማረፊያና ምቹ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ሆነው መልማታቸውን ገልጸዋል፡፡

የልማት ስራዎቹ እንደ ከተማም ሆነ እንደ ሀገር አዲስ እሳቤና ምሳሌ መሆናቸውን አንስተው፤ ፕሮጀክቶቹ ከተማዋን እንደ ስሟ አዲስ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ውጤት ማሳያ ናቸው ብለዋል፡፡

ይህንኑ አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የመዲናዋ ነዋሪዎች እንደገለጹት፤ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችና የኮሪደር ልማቶች የከተማዋን ገጽታ በእጅጉ ከመቀየራቸው በላይ ለነዋሪዎች የመዝናኛ አማራጭ ሆነዋል፡፡

በከተማዋ በቀጨኔ ወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት ሲዝናኑ ያገኘናቸው አቶ መሀመድ ተመስገን፤ አካባቢው ከዚህ ቀደም ለወንጀል ምቹ የሆነ፣ ለጎርፍ የተጋለጠና ለማየት የማይመች እንደነበር አስታውሰዋል፡፡


በአካባቢው ለረጅም ጊዜ ከመኖራቸው አንጻር የወንዙ ዳርቻ በዚህ ደረጃ ተለውጦ መመልከታቸው እንዳስገረማቸው ተናግረዋል፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪ አቶ ብርሃኑ ካሳዬ፤ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት የተበከሉና ቆሻሻ መጣያ የነበሩ ወንዞችን ያከመና ወደ ቀደመ ማንነታቸው የመለስ ነው ብለዋል።


ስፍራዎቹ አሁን ለህጻናት፣ ወጣቶችና አዋቂዎች የመዝናኛ አማራጭ ከመሆን ባለፈ መንፈስን የሚያድሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የአራዳ ክፍለ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ ሂሩት አድነው፤ በወንዝ ዳር የተሰሩ የልማት ስራዎች ወንዞችን ከቆሻሻ መጣያነትና ከመጥፎ ጠረን በማላቀቅ ምቹና ሳቢ እንዲሆኑ ማስቻሉን ጠቅሰዋል።


ነዋሪዎቹ እንደገለጹት፤ በኮሪደር ልማቱ የተገነቡ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶች፣ ፓርኮችና የመዝናኛ ስፍራዎች የከተማዋን ገጽታ በእጅጉ የቀየሩና ለነዋሪዎች የመዝናኛ አማራጭ የፈጠሩ ናቸው፡፡

በመዲናዋ የተገነቡ የልማት ስራዎች የታለመላቸውን አገልግሎት በዘላቂነት እንዲሰጡ የመጠበቅና የመንከባከብ ሃላፊነት ከሁሉም የሚጠበቅ ግዴታ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026