🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የተገነቡ የወንዝ ዳርቻና የኮሪደር ልማቶችን የመጠበቅና የመንከባከብ ሃላፊነት የሁላችንም ነው ሲሉ የመዲናዋ ነዋሪዎች ገለጹ።
አዲስ አበባን ዘመናዊ ለነዋሪዎቿ ምቹ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለማድረግ እየተከናወኑ ከሚገኙ ስራዎች መካከል የወንዝ ዳርቻ ልማት አንዱ ነው፡፡
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በቅርቡ የቀበናና ግንፍሌ ወንዝ ዳርቻ ልማት ሂደትን በተመለከቱበት ወቅት እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቶቹ ወንዞችና ዳርቻዎቻቸውን ከስጋትና ከብክለት ነጻ በማድረግ ስነ-ምህዳሯን የጠበቀች፤ ውብና ፅዱ ከተማ ለመፍጠር እያስቻሉ ነው፡፡

በከተማዋ ተረስተው የነበሩና ከልማት ተገልለው የቆዩ የወንዝ ዳርቻዎች ዛሬ ላይ የብዙዎች አይን ማረፊያና ምቹ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ሆነው መልማታቸውን ገልጸዋል፡፡
የልማት ስራዎቹ እንደ ከተማም ሆነ እንደ ሀገር አዲስ እሳቤና ምሳሌ መሆናቸውን አንስተው፤ ፕሮጀክቶቹ ከተማዋን እንደ ስሟ አዲስ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ውጤት ማሳያ ናቸው ብለዋል፡፡
ይህንኑ አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የመዲናዋ ነዋሪዎች እንደገለጹት፤ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችና የኮሪደር ልማቶች የከተማዋን ገጽታ በእጅጉ ከመቀየራቸው በላይ ለነዋሪዎች የመዝናኛ አማራጭ ሆነዋል፡፡
በከተማዋ በቀጨኔ ወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት ሲዝናኑ ያገኘናቸው አቶ መሀመድ ተመስገን፤ አካባቢው ከዚህ ቀደም ለወንጀል ምቹ የሆነ፣ ለጎርፍ የተጋለጠና ለማየት የማይመች እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

በአካባቢው ለረጅም ጊዜ ከመኖራቸው አንጻር የወንዙ ዳርቻ በዚህ ደረጃ ተለውጦ መመልከታቸው እንዳስገረማቸው ተናግረዋል፡፡
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪ አቶ ብርሃኑ ካሳዬ፤ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት የተበከሉና ቆሻሻ መጣያ የነበሩ ወንዞችን ያከመና ወደ ቀደመ ማንነታቸው የመለስ ነው ብለዋል።

ስፍራዎቹ አሁን ለህጻናት፣ ወጣቶችና አዋቂዎች የመዝናኛ አማራጭ ከመሆን ባለፈ መንፈስን የሚያድሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የአራዳ ክፍለ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ ሂሩት አድነው፤ በወንዝ ዳር የተሰሩ የልማት ስራዎች ወንዞችን ከቆሻሻ መጣያነትና ከመጥፎ ጠረን በማላቀቅ ምቹና ሳቢ እንዲሆኑ ማስቻሉን ጠቅሰዋል።

ነዋሪዎቹ እንደገለጹት፤ በኮሪደር ልማቱ የተገነቡ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶች፣ ፓርኮችና የመዝናኛ ስፍራዎች የከተማዋን ገጽታ በእጅጉ የቀየሩና ለነዋሪዎች የመዝናኛ አማራጭ የፈጠሩ ናቸው፡፡
በመዲናዋ የተገነቡ የልማት ስራዎች የታለመላቸውን አገልግሎት በዘላቂነት እንዲሰጡ የመጠበቅና የመንከባከብ ሃላፊነት ከሁሉም የሚጠበቅ ግዴታ መሆኑን አንስተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025