🔇Unmute
አዳማ ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያሉትን ተግዳሮቶች በመፍታት በዘርፉ መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት ቅንጅታዊ አሰራር እንደሚጠናከር ተገለጸ።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የመሠረተ ልማት ክላስተር የስድስት ወራት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ዛሬ በአዳማ ተካሂዷል።
በዚህ ወቅት የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) እንዳስታወቁት በአምራች ኢንዱስትሪው ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች ከበርካታ ባለድርሻ አካላት ጋር የተያያዙ ናቸው።

በዚህም ምክንያት የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎች የአቅማቸውን ያህል እያመረቱ እንዳልነበር ተናግረዋል።
ይህን ችግር ለመፍታት እንደ ሀገር የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን በመፍጠር በኢንዱስትሪ ዘርፍ በአጭር ጊዜ መሠረታዊ የሆኑና ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል።
ይህንን የበለጠ ለማሳለጥ እንዲቻልም በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የመሠረተ ልማትን ጨምሮ ስድስት ክላስተሮች ተቋቁመው በየደረጃው በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በየደረጃው ያሉ የመንግስት አካላት የአምራች ኢንዱስትሪ ማነቆዎችን በመለየት እንዲፈቱ እገዛ ማድረጋቸውን አንስተዋል።
ይህም የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ለመሳብ፣ በሀገር ውሰጥ ያሉ አምራች ኢንዱስትሪዎች በአቅማቸው ልክ ማምረት እንዲችሉ እና ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ እንዲችሉ ያደርጋል ብለዋል።
እንዲሁም አምራች ኢንዱስትሪው አገር የምትጠብቀውን ውጤት እንዲያስመዘግቡና በዘርፉ መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት ምቹ መደላድል እየተፈጠረ እንደሚገኝ አውስተዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት ኃላፊና የሚኒስትሩ ተወካይ አቶ ዮናስ መኩሪያ በበኩላቸው፤ አምራች ኢንዱስትሪውን ለማጠናከርና ለማስፋፋት በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት የተቀናጀ ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በቅንጅታዊ አሰራር መፍትሄዎችን በመስጠት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል።
በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ ወይዘሮ የሮሰን ኪሲ፣ ክላስተሩ ባለፉት ስድስት ወራት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች መሰረተ ልማት አቅርቦትን ለማሻሻል የተለያዩ ተግባራት ማከናወኑን ገልጸዋል።

ለ176 ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል፤ ለ522 ኢንዱስትሪዎች ደግሞ አነስተኛ ኃይል እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉንም አውስተዋል።
እንዲሁም በስምንት ክልሎች 23 ሺህ ሄክታር መሬት ለኢንዱስትሪ ተከልሎ ለአልሚዎች እየተላለፈ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
አምስት ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ከዋናው መንገድ ጋር ለማገናኘት እና በተለያዩ አካባቢዎች ግንባታቸው እየተካሄዱ ለሚገኙ ሶስት ደረቅ ወደቦች ክትትልና ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል።

ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ አቶ ደሴ አስማረ ፤ ለአምራች ኢንዱስትሪው ክላስተር ተቋቁሞ በቅንጅት መሰራቱ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ ትልቅ መነቃቃት እና የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግብ ምቹ መደላድል መፍጠሩን አውስተዋል።
ከመድረኩ ጎን ለጎን ተሳታፊዎቹ የአዳማ ልዩ ኢኮኖሚ ዞንን ጎብኝተዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026