🔇Unmute
ባህር ዳር፣ጥር 9/2018(ኢዜአ)፦የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር በከተማዋ የሚስተዋለውን የትራንስፖርት ችግር ለማቃለል በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ዘመናዊ የህዝብ ማጓጓዣ አውቶቡሶችን ሥራ አስጀመረ።
ዛሬ የአውቶቡሶቹ ርክክብ ሥነ ስርአት የተካሄደው የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፣የምስራቅ እዝ ዋና አዛዥና የቀጠናው የፀጥታ ግብረ ሃይል ሰብሳቢ ሌተናል ጄነራል መሀመድ ተሰማና ሌሎች ሥራ ሃላፊዎች በተገኙበት ነው።
የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው በዚህ ወቅት እንደገለጹት፦ የከተማዋን ዘመናዊነት ከሚያረጋግጡ ተግባራት መካከል ዘመናዊና የተሳለጠ የትራንስፖርት አገልግሎት አንዱ ነው።
በዚህም ከተማ አስተዳደሩ ዘመኑን የዋጁና በኤሌክትሪክ የሚሰሩ አስር አውቶብሶችን በመግዛት ዛሬ ሥራ ማስጀመሩን ገልፀዋል።

ይህም የከተማዋን ህዝብ የትራንስፖርት ችግር ከመፍታት ባለፈ የቱሪዝም ማዕከልና የኢንቨስትመንት ተመራጭ ከተማ ለማድረግ የተጀመረውን ሥራ እንደሚያጠናክር አስረድተዋል።
በተለይም አውቶቡሶቹ በከተማዋ በኮሪደር ልማት ከተገነባው ሰፊ የአስፋልት መንገድ ጋር የተጣጣመ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ዘመኑን የሚመጥንና በአነስተኛ ክፍያ ለህብረተሰቡ የትራንስፖርት አገልግሎት ማቅረብ ወሳኝና የከተማ እድገት መገለጫ እንደሆኑም አመልክተዋል።
በከተማዋ ከዚህ ቀደም ከ20 በላይ አውቶብሶች ለህብረተሰቡ አገልግሎት ሲሰጡ እንደነበር ጠቁመው፣ የኤሌክትሪክ አውቶብሶች መጨመር የባህር ዳርን ስማርት ከተማነት ለማረጋገጥ የተያዘው ግብ ለማሳካት ያግዛል ብለዋል።
የቢኬጅ (በላይነህ ክንዴ ግሩፕ) ባለቤትና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ በላይነህ ክንዴ በእለቱ እንደገለጹት፥ ቢኬጅ እንደሀገር በተለያዩ የልማት ሥራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ ያለ ድርጅት ነው ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ ትኩረት የተሰጠውን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለማሳካትም አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማስገባት ጭስ አልባና ለብዙ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ አውቶቡሶችን በመገጣጠም እያከፋፈለ ይገኛል ብለዋል።
አውቶቡሶቹ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ እንደመሆናቸው መጠን ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ መሳካት ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸው ገልጸው፣ በሀገር ውስጥ መመረታቸው መለዋወጫ በቀላሉ ለማግኘት እንደሚያስችል ተናግረዋል።
በአውቶቡሶቹ ርክክብ ላይ የተገኙት አማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በኤሌክትሪክ የሚሰሩትን አውቶብሶች ሥራ አስጀምረዋል።
በሥነ-ስርዓቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ሌሎች አመራሮችና የከተማዋ ነዋሪዎችም ተገኝተዋል።
#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025