የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ከ27 ሺህ በላይ የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች ተደርገዋል -ኢመደአ

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1 /2018 (ኢዜአ) ፦የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) በስድስት ወራት ከተሞከሩ 27 ሺህ 773 የሳይበር ጥቃቶች 99 ነጥብ 03 በመቶ የሚሆነውን ማክሸፍ ተችሏል አለ።

ተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሂዷል።

የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተቀያየሩ የመጡትን የሳይበር ጥቃት ባህሪያት ግምት ውስጥ በማስገባት የመከላከል አቅማችን እየዘመነ ይገኛል ብለዋል፡፡

የሳይበር ደህንነት ሥጋቶችን ቀድሞ ለመለየትና ምላሽ ለመስጠት የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶችን ለማበልጸግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራተጂ መሠረት የሚሆኑ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰው የመንግሥት ተቋማትን ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ አሠራራቸውን ዲጂታላይዝ የሚያደርጉ የቴክኖሎጂዎችን እንዲታጠቁ መደረጉን ገልጸዋል።

ለአብነትም ገቢዎች ሚኒስቴር የኢ-ኢንቮይስ፣ አዲስ አበባ ገቢዎች የሰውነት ላይ ካሜራ፣ እንዲሁም ፌደራል ፖሊስ የተቀናጀ የሰው ሀብትና የሰነድ አስተዳደር ሲስተሞችን በማልማት አገልግሎታቸውን እንዲያዘምኑ መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡

በኢትዮጵያ የሚሰነዘሩ የሳይበር ጥቃቶችን ለማክሸፍ እየተሰራ መሆኑን አንስተው፤ በስድስት ወራት ከተሰነዘሩ 27 ሺህ 773 የሳይበር ጥቃቶች ውስጥ 99 ነጥብ 03 በመቶ የሚሆነውን ማለትም 27 ሺህ 505ቱን ማክሸፍ መቻሉን ገልጸዋል።

የዲጂታል ፎረንሲክ ምርመራን በተመለከተ አስተዳደሩ ከቀረቡለት 253 የምርመራ ጥያቄዎች ውስጥ ለ245ቱ ምላሽ መሰጠቱን የኢመደአ መረጃ አመልክቷል፡፡

የኢዜአ የዲጂታል ሚዲያ ገጾች ፦ https://linktr.ee/ENADigital

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026