🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ):-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሰዎች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ ቦጋለ ቦሼ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎች በነጻነት ለመንቀሳቀስ የሚያስችላቸው ነው።
መታወቂያው የዜጎችን ትክክለኛ ማንነት ለመለየትና የወንጀል ድርጊቶችን በመከላከል ለማህበረሰቡ ሁለንተናዊ ዋስትና መረጋገጥ ጠቀሜታ እንዳለውም አንስተዋል።
በክልሉም ነዋሪዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
እስካሁንም መታወቂያውን ለማግኘት ከተመዘገቡት 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሰዎች ውስጥ 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሚሆኑት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡
በክልሉ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተሰራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ መታወቂያውን ለመውሰድ የተመዘገቡ ነዋሪዎች ቁጥር እያደገ መምጣቱን ገልጸው፣ "በበጀት ዓመቱ ለ6 ሚሊዮን ዜጎችን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ ነው" ብለዋል።
የፋይዳ መታወቂያ አይነስውራን አገልግሎት ለማግኘት ይደርስብን የነበረውን እንግልት በመቀየር ትልቅ ለውጥ አምጥቷል ያለው ደግሞ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ ተማሪ መሸሻ ማንዳዶ ነው።
መታወቂያው በተለይ እንደእሱ አይነስውራን ለሆኑ ዜጎች ተደራሽ በመደረጉ እንግልቶችን ከማስቀረት ባለፈ በነፃነት ለመንቀሳቀስ አስችሎናል ነው ያለው።
አቶ መሳይ ሳሙኤል የተባሉ ሌላው አስተያየት ሰጪ በበኩላቸው "የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በንግድ ሥራችን ላይ ሊደረስ የሚችል መጭበርበርን እየታደገ ነው" ብለዋል።
መታወቂያው የዜጎችን ትክክለኛ መረጃ በተሻለ መንገድ እንዲያዝ በማድረጉ ወንጀልና ወንጀለኞችን በቀላሉ ለመከላከል የጎላ አስተዋጾ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ቴዎድሮስ ዘካሪያስ በበኩላቸው፤ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸው በንግድም ሆነ በሌሎች ተግባራት ደሕንነቱ የተጠበቀ እንቅስቃሴ ለማድረግ እንደረዳቸው ተናግረዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026