የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሰዎች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ወስደዋል-ቢሮው

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ሶዶ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ):-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሰዎች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ ቦጋለ ቦሼ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎች በነጻነት ለመንቀሳቀስ የሚያስችላቸው ነው።

መታወቂያው የዜጎችን ትክክለኛ ማንነት ለመለየትና የወንጀል ድርጊቶችን በመከላከል ለማህበረሰቡ ሁለንተናዊ ዋስትና መረጋገጥ ጠቀሜታ እንዳለውም አንስተዋል።

በክልሉም ነዋሪዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

እስካሁንም መታወቂያውን ለማግኘት ከተመዘገቡት 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሰዎች ውስጥ 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሚሆኑት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡

በክልሉ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተሰራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ መታወቂያውን ለመውሰድ የተመዘገቡ ነዋሪዎች ቁጥር እያደገ መምጣቱን ገልጸው፣ "በበጀት ዓመቱ ለ6 ሚሊዮን ዜጎችን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ ነው" ብለዋል።

የፋይዳ መታወቂያ አይነስውራን አገልግሎት ለማግኘት ይደርስብን የነበረውን እንግልት በመቀየር ትልቅ ለውጥ አምጥቷል ያለው ደግሞ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ ተማሪ መሸሻ ማንዳዶ ነው።

መታወቂያው በተለይ እንደእሱ አይነስውራን ለሆኑ ዜጎች ተደራሽ በመደረጉ እንግልቶችን ከማስቀረት ባለፈ በነፃነት ለመንቀሳቀስ አስችሎናል ነው ያለው።

አቶ መሳይ ሳሙኤል የተባሉ ሌላው አስተያየት ሰጪ በበኩላቸው "የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በንግድ ሥራችን ላይ ሊደረስ የሚችል መጭበርበርን እየታደገ ነው" ብለዋል።

መታወቂያው የዜጎችን ትክክለኛ መረጃ በተሻለ መንገድ እንዲያዝ በማድረጉ ወንጀልና ወንጀለኞችን በቀላሉ ለመከላከል የጎላ አስተዋጾ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ቴዎድሮስ ዘካሪያስ በበኩላቸው፤ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸው በንግድም ሆነ በሌሎች ተግባራት ደሕንነቱ የተጠበቀ እንቅስቃሴ ለማድረግ እንደረዳቸው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026