🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ):-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሰዎች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ ቦጋለ ቦሼ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎች በነጻነት ለመንቀሳቀስ የሚያስችላቸው ነው።
መታወቂያው የዜጎችን ትክክለኛ ማንነት ለመለየትና የወንጀል ድርጊቶችን በመከላከል ለማህበረሰቡ ሁለንተናዊ ዋስትና መረጋገጥ ጠቀሜታ እንዳለውም አንስተዋል።
በክልሉም ነዋሪዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
እስካሁንም መታወቂያውን ለማግኘት ከተመዘገቡት 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሰዎች ውስጥ 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሚሆኑት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡
በክልሉ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተሰራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ መታወቂያውን ለመውሰድ የተመዘገቡ ነዋሪዎች ቁጥር እያደገ መምጣቱን ገልጸው፣ "በበጀት ዓመቱ ለ6 ሚሊዮን ዜጎችን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ ነው" ብለዋል።
የፋይዳ መታወቂያ አይነስውራን አገልግሎት ለማግኘት ይደርስብን የነበረውን እንግልት በመቀየር ትልቅ ለውጥ አምጥቷል ያለው ደግሞ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ ተማሪ መሸሻ ማንዳዶ ነው።
መታወቂያው በተለይ እንደእሱ አይነስውራን ለሆኑ ዜጎች ተደራሽ በመደረጉ እንግልቶችን ከማስቀረት ባለፈ በነፃነት ለመንቀሳቀስ አስችሎናል ነው ያለው።
አቶ መሳይ ሳሙኤል የተባሉ ሌላው አስተያየት ሰጪ በበኩላቸው "የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በንግድ ሥራችን ላይ ሊደረስ የሚችል መጭበርበርን እየታደገ ነው" ብለዋል።
መታወቂያው የዜጎችን ትክክለኛ መረጃ በተሻለ መንገድ እንዲያዝ በማድረጉ ወንጀልና ወንጀለኞችን በቀላሉ ለመከላከል የጎላ አስተዋጾ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ቴዎድሮስ ዘካሪያስ በበኩላቸው፤ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸው በንግድም ሆነ በሌሎች ተግባራት ደሕንነቱ የተጠበቀ እንቅስቃሴ ለማድረግ እንደረዳቸው ተናግረዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026