የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የህብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ የተጀመሩ ስራዎች ውጤት እያመጡ ነው -አቶ አወሉ አብዲ

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሞጆ ፤የካቲት 5/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የህብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ የተጀመሩ ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ ገለፁ።

የሞጆ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ወደስራ ገብቷል።


የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አወሉ አብዲ ማዕከሉን መርቀው አገልግሎት ሲያስጀምሩ አንደገለጹት በክልሉ የመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ ለማድረግ ለዲጂታላይዜሽን ትኩረት ተሰጥቷል።

ለዚህም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫን ተደራሽ ለማድረግ በመጀመሪያ ምዕራፍ በአዳማ፣ ሻሸመኔ፣ ሸገር፣ ቢሾፍቱና ጂማ ከተሞች ወደስራ ማስገባቱን አስታውሰዋል።

ተግባሩን በማጠናከርም ወደ 26 ከተሞች እየተስፋፋ መሆኑን ጠቅሰው የዛሬ የሞጆ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ መጀመር የዚሁ አካል መሆኑን አስረድተዋል።


የከተማ አስተዳደሩ የህንፃ ግንባታውን በፍጥነት በማጠናቀቅ ከወረቀት ንኪኪ ነፃ የሆነ ዲጂታል አገልግሎት ማስጀመር መቻሉን ገልጸዋል።

የማዕከሉ ሙያተኞችም ህብረተሰቡን በስነ-ምግባርና በታማኝነት በማገልገል የአገልግሎት አሰጣጥ ዕርካታን ማረጋገጥ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል ።

በሶስተኛ ምዕራፍ በክልሉ 60 ከተሞች የመሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ለማስጀመር ግብ መቀመጡን አንስተዋል።

በቀጣይ የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን፣ የኮሪደር ልማት፣ የገቢ አሰባሰብና የልማት ስራዎች ማጠናከር ላይ በትኩርት ይሰራል ብለዋል።

የሞጆ ከተማ ከንቲባ አቶ ገዛሊ ሀሹ በበኩላቸው በከተማዋ መልካም አስተዳደርን በማስፈን ቀልጣፋ የህዝብ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እይተደረገ ብለዋል።

ለዚህም በተለያዩ ተቋማት ሲሰጥ የነበረውን የመንግስት አገልግሎቶች በመሶብ የአንድ አገልግሎት ማእከል መስጫ በማሰባሰብ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር መዘርጋቱ አንስተዋል።

''ማዕከሉ የህዝቡ ዕንግልት ከማስቀረት ባለፈ የአገልግሎት አሰጣጥ ማነቆዎችን የሚቀርፍ ነው'' ያሉት ከንቲባው ጥራት ያለው ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ እንዲቻል የማዕከሉ ሙያተኞችን በስነ ምግባር፣ በትምህርት ዝግጅት መመደቡን ተናግረዋል ።

ማእከሉ የ23 መስሪያ ቤቶች፣ በ12 መስኮቶች 106 አገልግሎቶች እየሰጠ ይገኛል ብለዋል።


የማእከሉን ስራ መጀመር አስመልክተው አስተያየት ከሰጡ የሞጆ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ አስቴር ቢራ እንደገለፁት ማእከሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ማዘመኑ እንግልትን የሚያስቀር ነው።

ይህም ጊዜና ገንዘባቸውን ከመቆጠብ ባለፈ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶችን በአንድ ቦታ አገልግሎት ማግኘት እንደሚያስችላቸው ጠቁመዋል።

ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ሙሉ ቸርነት በበኩላቸው መስተዳድሩ የህዝቡን ቅሬታ ለመፍታት መሶብ የአንድ ማእክል አገልግሎትን ስራ ማስጀመሩ የሚበረታታ ነው ብለዋል።

ባንኮች ጨምሮ በአገልግሎት መስጫ ማዕከሉ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸው ከመስሪያ ቤት ወደ መስሪያ ቤት የነበረውን ምልልስ በማሳጠር ፈጣን አገልግሎት እንድያገኙ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026