የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በምግብ ራስን ከማስቻል ባለፈ ከተረጂነት ለመውጣት እገዛ እያደረገ ነው

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባምንጭ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ) :- በጋሞ ዞን የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በምግብ ራስን ከማስቻል ባለፈ ከተረጂነት ለመውጣት እገዛ እያደረገ መሆኑ ተገለጸ።

በዞኑ ከ1 ሺህ 300 ሄክታር በላይ የበጋ ስንዴ በአርሶ አደሮችና በባለሀብቶች ማሳ እየለማ የሚገኝ ሲሆን የሚጠበቀውን ምርት ለማግኘት የሚያስችል የተባይ ቁጥጥርና እንክብካቤ እየተደረገ እንደሚገኝም ተመልክቷል።

የበጋ ስንዴ ልማት ከተጀመረ ወዲህ ከተረጂነት ወጥተን በምግብ ራሳችንን ለመቻል እየተደረገ ባለው ጥረት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ያሉት ደግሞ በቁጫ ወረዳ ፋንጎ ቀበሌ አርሶ አደር ሚሊዮን በየነ ናቸው።

ከበጋ ስንዴ በሚገኝ ጥቅም ልጆቻችንን ለማስተማርና ኑሮአችን ለመለወጥ ብሎም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ሳንቸገር እንድንከውን አቅም ሆኖናል ብለዋል።

በሁለት ሄክታር መሬት ላይ ስንዴን በመስኖ እያለሙ መሆናቸውን ጠቅሰው የእንክብካቤና የቁጥጥር ስራ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የግብርና ባለሙያዎች ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እያደረጉ መሆኑን ገልጸው በቴክኖሎጂ በመታገዝ ከአንድ ሄክታር ከ40 ኩንታል በላይ ለማግኘት ማቀዳቸውን ተናግረዋል።

በጋሞ ዞን በምዕራብ አባያ ወረዳ አልጌ ቀበሌ በ20 ሄክታር መሬት ላይ ስንዴ እያለማ የሚገኘው ሳውዝ አግሮ ኢንዱስትሪ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ብሩክ ማማ ምርቱ በጥሩ ቁመና ላይ መሆኑን ገልጸዋል።

ወረዳው የምርጥ ዘር እና የማዳበሪያ እንዲሁም የሙያ ድጋፍ ማድረጉን ጠቅሰው የስንዴ ምርቱ በምግብ ራስን የመቻል ዕድልን የማስፋት አማራጭ እንደሚሰጥም አስረድተዋል።

ድርጅቱ ከዛሬ 5 ዓመት ጀምሮ ስንዴን በመስኖ በስፋት በማምረት ለአካባቢው መነቃቃት የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ጠቅሰው ከዘንድሮው ምርትም ከአንድ ሄክታር 45 ኩንታል ለማግኘት አቅደን እየሠራን እንገኛለን ብለዋል።

የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ባለሙያ አቶ ሳሙኤል ኤርቦ በበኩላቸው የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ቴክኖሎጂን በአግባቡ እንዲጠቀም ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ስራ የአርሶ አደሩን የግብርና ባህል በመቀየር ጥሪት እንዲያፈሩና ኑሮአቸውን እንዲያሻሽሉ እገዛ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል።

የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ሃላፊ አቶ ወርቅነህ ካልሳ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት የበጋ መስኖ ስንዴ በምግብ ራስን የመቻል ራዕይን በተጨባጭ እያሳካው ይገኛል ብለዋል።

በተለይ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አርሶ አደሮች ከተረጂነት ወጥተው የምግብ ሉዓላዊነታቸውን እንዲያረጋግጡ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በዞኑ በተያዘው በጋ ወቅት 1 ሺህ 380 ሄክታር መሬት ስንዴ በመስኖ እየለማ እንደሚገኝ አመልክተው ከዚህም ከ46 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት የሚጠበቅ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025