የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የተከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር፤ የካቲት 5/2018(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የተከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት የህዝብን ተጠቃሚነት በተጨባጭ ያረጋገጡ መሆናቸውን የክልሉ ምክር ቤት አባላት ገለጹ።

ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመጠቀም ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ እንደሚገባም ጠቁመዋል።

እየተካሄደ የሚገኘው የሐረሪ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ አመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤ የአስፈፃሚውንና የማዘጋጃ ቤት አገልግሎት የግማሽ በጀት አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ተወያይቷል።

የምክር ቤቱ አባላት በወቅቱ እንዳሉት፤ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የተከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት የህዝብን ተጠቃሚነት በተጨባጭ ያረጋገጡ ናቸው።


የክልሉን ሁለንተናዊ ዕድገት እና የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራትም የበለጠ ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በተከናወኑ ተግባራት በማሕበራዊና በምጣኔ ሃብት ዘርፎች እንዲሁም በኮሪደር ልማት ውጤቶች መምጣታቸውን ገልጸዋል።

የክልሉ ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ ቅንጅታዊ አሰራርነ ማጠናከርና ዘላቂነት ያለው ልማት ማረጋገጥ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።


የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች መሰራታቸውን አንስተዋል።

በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት 3 ቢሊየን 815 ሚሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን አንስተው የተገኘው ገቢ ከአምና ተመሳሳይ ወቅት አንፃር በ29 በመቶ ብልጫ አለው ብለዋል።

ነገር ግን በግማሽ በጀት አመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው እና የክልሉ ኢኮኖሚ ከሚያመነጨው ሀብት አንፃር የሚፈለገውን ገቢ የመሰብሰቡ ስራ ትኩረት እንደሚጠይቅ ገልፀዋል።

በክልሉ ቀጣይነት ያለው የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጠና ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጣ ለመሰብሰብ በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ጉባኤ በክልሉ ርዕሰ-መስተዳደር ኦርዲን በድሪ የቀረበውን ሪፖርት በሙሉ ድምፅ ያፀደቀ ሲሆን በአሁን ሰአት በተለያዩ ረቂቅ አዋጆች ላይ እየተወያየ ይገኛል።

ምክር ቤቱ በመደበኛ ጉባኤው ከ743 ሚሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ያጸደቀ ሲሆን ተጨማሪ በጀቱለመደበኛና ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ እንደሚውልም ተመላክቷል።

ጉባዔው በተጨማሪም በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ በማሳለፍ ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026