የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በከተማዋ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ባለፉት ስድስት ወራት 14 ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ ገብተዋል

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ የካቲት 5/2018(ኢዜአ)፦በባህር ዳር ከተማ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 14 ኢንዱስትሪዎች ወደ ምርት መግባታቸውን የከተማዋ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።

የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ የአስተዳደሩ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በባህር ዳር ከተማ ወደ ሥራ የገቡ ኢንዱስትሪዎችን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ ብርሃን ንጉሴ፤ የ“ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት” ንቅናቄ የከተማዋን የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ማነቃቃቱን ተናግረዋል።


ንቅናቄውን ተከትሎ ባለፉት ስድስት ወራት ለኢንዱስትሪዎች በተደረገ ድጋፍና ክትትል 14 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መግባታቸውን ገልጸዋል።

በባህር ዳር ከተማ 73 ነባርና አዲስ ኢንዱስትሪዎች ተኪ ምርት ላይ አተኩረው እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰው፣ ኢንዱስትሪዎቹ ባለፉት ስድስት ወራት ከ66 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ማዳን ችለዋል ነው ያሉት።

በከተማዋ አራት ኢንዱስትሪዎች ምርቶቻቸውን በቀጥታ ወደ ውጪ በመላክ ከ3 ነጥብ 1ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ገቢ ማስገኘታቸውንም የመምሪያ ሃላፊዋ አመልክተዋል።


እንደሃላፊዋ ገለጻ፤የኢትዮጵያ ታምራት ንቅናቄ የከተማዋን የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ከማነቃቃት በላይ ከ2 ሺህ 400 ለሚልቁ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ አስችሏል።

በከተማዋ አጠቃላይ 273 ኢንዱስትሪዎች በማምረት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው መንግስት ለኢንዱስትሪዎቹ ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል።

የኤም.ኤስ.ሲ ቢዝነስ ግሩፕ የባህር ዳር ቀጣና ሥራ አስኪያጅ አበረ አበራ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ፋብሪካው በእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያና በምግብ ዘይት ማምረት ላይ ተሰማርቶ እየሰራ ይገኛል።


ፋብሪካው በቀን እስከ 200 ሺህ ሊትር የምግብ ዘይት የማምረት አቅም እንዳለውና በአሁኑ ወቅትም ተኪ ምርት በማምረት የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት በኩል የድርሻውን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።


በከተማ አስተዳደሩ እየተደረገላቸው ያለው ክትትልና ድጋፍ የሚያስመሰግንና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነው ያሉት ደግሞ የአማጋ ባህር ዳር ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ሥራ አስኪያጅ አማረ መብራቴ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026