🔇Unmute
ባህር ዳር፤ የካቲት 5/2018(ኢዜአ)፦በባህር ዳር ከተማ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 14 ኢንዱስትሪዎች ወደ ምርት መግባታቸውን የከተማዋ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።
የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ የአስተዳደሩ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በባህር ዳር ከተማ ወደ ሥራ የገቡ ኢንዱስትሪዎችን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ ብርሃን ንጉሴ፤ የ“ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት” ንቅናቄ የከተማዋን የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ማነቃቃቱን ተናግረዋል።

ንቅናቄውን ተከትሎ ባለፉት ስድስት ወራት ለኢንዱስትሪዎች በተደረገ ድጋፍና ክትትል 14 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መግባታቸውን ገልጸዋል።
በባህር ዳር ከተማ 73 ነባርና አዲስ ኢንዱስትሪዎች ተኪ ምርት ላይ አተኩረው እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰው፣ ኢንዱስትሪዎቹ ባለፉት ስድስት ወራት ከ66 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ማዳን ችለዋል ነው ያሉት።
በከተማዋ አራት ኢንዱስትሪዎች ምርቶቻቸውን በቀጥታ ወደ ውጪ በመላክ ከ3 ነጥብ 1ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ገቢ ማስገኘታቸውንም የመምሪያ ሃላፊዋ አመልክተዋል።

እንደሃላፊዋ ገለጻ፤የኢትዮጵያ ታምራት ንቅናቄ የከተማዋን የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ከማነቃቃት በላይ ከ2 ሺህ 400 ለሚልቁ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ አስችሏል።
በከተማዋ አጠቃላይ 273 ኢንዱስትሪዎች በማምረት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው መንግስት ለኢንዱስትሪዎቹ ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኤም.ኤስ.ሲ ቢዝነስ ግሩፕ የባህር ዳር ቀጣና ሥራ አስኪያጅ አበረ አበራ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ፋብሪካው በእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያና በምግብ ዘይት ማምረት ላይ ተሰማርቶ እየሰራ ይገኛል።

ፋብሪካው በቀን እስከ 200 ሺህ ሊትር የምግብ ዘይት የማምረት አቅም እንዳለውና በአሁኑ ወቅትም ተኪ ምርት በማምረት የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት በኩል የድርሻውን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።

በከተማ አስተዳደሩ እየተደረገላቸው ያለው ክትትልና ድጋፍ የሚያስመሰግንና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነው ያሉት ደግሞ የአማጋ ባህር ዳር ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ሥራ አስኪያጅ አማረ መብራቴ ናቸው።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026