🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና ሩሲያ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ግንኙነት ማጠናከር የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል።
የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ከሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ አጋርነት ዳይሬክተር ታትያና ዶቭጋሌንኮ ጋር በተቋሙ መቀመጫ ጅቡቲ ተወያይተዋል።
በውይይቱ ወቅት ኢጋድ እና ሩሲያ በፖሊሲና ደኅንነት፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን፣ ሳይንስ እና ትምህርት ዘርፎች ትብብር ማጎልበት የሚያስችላቸውን ስምምነት እና የድርጊት መርሐ-ግብር ተፈራርመዋል።
ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ ጉዳዮች ተቀራርበው ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026