የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ ናቸው - ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር)

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እና የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ጠንካራ ፍላጎት እንዳላቸው የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተመራው የኢትዮጵያ ልዑክ በአዘርባጃን ያደረገውን ይፋዊ የስራ ጉብኝት አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው የአዘርባጃን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አካዳሚን መጎብኘቱን ገልጸዋል።

አካዳሚው በአንድ ዓመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ የትምህርቱ ዘርፍን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የሰው ሰራሽ አስተውሎት ተደራሽነት በማስፋት ረገድ ውጤታማ ስራ ማከናወኑን ከጉብኝቱ መረዳት መቻሉን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከስድስት ዓመታት በፊት መቋቋሙንና ውጤታማ ተግባራት እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በጉብኝቱ ወቅት በምርምር እና ዳታ ልውውጥ ላይ በትብብር ለመስራት በሀገራቱ መካከል መግባባት ላይ መደረሱን ነው የተናገሩት።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው የአዘርባጃን የሕዝብ አገልግሎት እና ማኅበራዊ ፈጠራ የመንግሥት ኤጀንሲ(ASAN) የፈጠራ ማዕከልን ጎብኝቷል።

አሳን የሚሰጠው አገልግሎት ከአንድ መሶብ አገልግሎት ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ በተለይም አገልግሎት አሰጣጡ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ መሆኑ ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ያለውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሰው ሰራሽ አስተውሎት እንዲታገዝና ጥራቱ እንዲያድግ በቀጣይ በትኩረት እንደሚሰራ አመልክተዋል።

የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በውይይታቸው በሰው ሰራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ በትብብር ለመስራት ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ጠቁመዋል።

ሀገራቱ በዘርፉ ልምድ ለመለዋወጥ ፍላጎት እንዳላቸውም ነው የተናገሩት።

አጠቃላይ ጉብኝቱ ኢትዮጵያ በቅርቡ ወደ ትግበራ ለገባው ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና ለዘርፉ ስራዎች አጋዥ አቅም እንደሚሆን ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026