የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ ናቸው - ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር)

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እና የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ጠንካራ ፍላጎት እንዳላቸው የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተመራው የኢትዮጵያ ልዑክ በአዘርባጃን ያደረገውን ይፋዊ የስራ ጉብኝት አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው የአዘርባጃን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አካዳሚን መጎብኘቱን ገልጸዋል።

አካዳሚው በአንድ ዓመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ የትምህርቱ ዘርፍን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የሰው ሰራሽ አስተውሎት ተደራሽነት በማስፋት ረገድ ውጤታማ ስራ ማከናወኑን ከጉብኝቱ መረዳት መቻሉን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከስድስት ዓመታት በፊት መቋቋሙንና ውጤታማ ተግባራት እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በጉብኝቱ ወቅት በምርምር እና ዳታ ልውውጥ ላይ በትብብር ለመስራት በሀገራቱ መካከል መግባባት ላይ መደረሱን ነው የተናገሩት።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው የአዘርባጃን የሕዝብ አገልግሎት እና ማኅበራዊ ፈጠራ የመንግሥት ኤጀንሲ(ASAN) የፈጠራ ማዕከልን ጎብኝቷል።

አሳን የሚሰጠው አገልግሎት ከአንድ መሶብ አገልግሎት ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ በተለይም አገልግሎት አሰጣጡ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ መሆኑ ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ያለውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሰው ሰራሽ አስተውሎት እንዲታገዝና ጥራቱ እንዲያድግ በቀጣይ በትኩረት እንደሚሰራ አመልክተዋል።

የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በውይይታቸው በሰው ሰራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ በትብብር ለመስራት ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ጠቁመዋል።

ሀገራቱ በዘርፉ ልምድ ለመለዋወጥ ፍላጎት እንዳላቸውም ነው የተናገሩት።

አጠቃላይ ጉብኝቱ ኢትዮጵያ በቅርቡ ወደ ትግበራ ለገባው ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና ለዘርፉ ስራዎች አጋዥ አቅም እንደሚሆን ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026