የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ዜጎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ዜጎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ እንደሚያስችል የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ዓሊ ተናገሩ።

ፋይዳ መታወቂያን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር ማስተሳሰር ከተጀመረ ወዲህ የተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ ነው

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የዲጂታል ጉዞ ቀጣይ 5 ዓመታት የሚመራበትን ''ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ'' በቅርቡ ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራ በሁለንተናዊ ዘርፍ በተለይም የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ አጋዥ ሚና ይኖረዋል።

በዚህ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ዓሊ እንዳሉት ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ስርዓቱን ለማዘመን እያገዘ ነው።

ዘመኑ ያፈራውን የዲጂታል አሰራር እውን በማድረግ በቀላሉ መግባባት፣ መረጃዎችን መቀባበልና በተለይም የግብይትም ሆነ ሌሎች አገልግሎቶችን በፍጥነት ለማግኝት እንደሚረዳ ነው የገለጹት።

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለማፋጠንና ከዘርፉም ቀጣይነት ባለው መልኩ ተጠቃሚ መሆን ያስችላል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት የስማርት ሲቲ ግንባታን ጨምሮ በየደረጃው ዲጂታል አሰራር በመተግበር እየታዩ ያሉ ለውጦች የሚያበረታቱ በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ሲሉም ገልጸዋል።

ስትራቴጂው መረጃዎችን በቀላሉ የመመዝገብ፣ የማስቀመጥና የመለዋወጥ ስራን ቀላልና ፈጣን ማድረጉንም ለአብነት አንስተዋል።

በዋናነት የመንግስት አገልግሎቶችን ቀልጣፋና ጥራት ያላቸው በማድረግ በኩል ሰፊ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026