የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ዜጎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ዜጎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ እንደሚያስችል የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ዓሊ ተናገሩ።

ፋይዳ መታወቂያን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር ማስተሳሰር ከተጀመረ ወዲህ የተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ ነው

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የዲጂታል ጉዞ ቀጣይ 5 ዓመታት የሚመራበትን ''ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ'' በቅርቡ ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራ በሁለንተናዊ ዘርፍ በተለይም የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ አጋዥ ሚና ይኖረዋል።

በዚህ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ዓሊ እንዳሉት ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ስርዓቱን ለማዘመን እያገዘ ነው።

ዘመኑ ያፈራውን የዲጂታል አሰራር እውን በማድረግ በቀላሉ መግባባት፣ መረጃዎችን መቀባበልና በተለይም የግብይትም ሆነ ሌሎች አገልግሎቶችን በፍጥነት ለማግኝት እንደሚረዳ ነው የገለጹት።

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለማፋጠንና ከዘርፉም ቀጣይነት ባለው መልኩ ተጠቃሚ መሆን ያስችላል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት የስማርት ሲቲ ግንባታን ጨምሮ በየደረጃው ዲጂታል አሰራር በመተግበር እየታዩ ያሉ ለውጦች የሚያበረታቱ በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ሲሉም ገልጸዋል።

ስትራቴጂው መረጃዎችን በቀላሉ የመመዝገብ፣ የማስቀመጥና የመለዋወጥ ስራን ቀላልና ፈጣን ማድረጉንም ለአብነት አንስተዋል።

በዋናነት የመንግስት አገልግሎቶችን ቀልጣፋና ጥራት ያላቸው በማድረግ በኩል ሰፊ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026